
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት 14 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) ገለጹ።
የከተማ አስተዳደሩ ለታማኝ ግብር ከፋዮች ያዘጋጀው የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማዋ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) እንደገለጹት ዘመናዊ፤ የበለጸገና ለኑሮ ምቹ የሆነ ከተማን ለመፍጠር ዜጎች ግብራቸውን በጊዜውና በአግባቡ መክፈል ይኖርባቸዋል።

ሸገር ከተማ ከመቋቋሟ በፊት ሲሰበሰብ የነበረው ገቢ ከ6 ቢሊዮን ብር ያልበለጠ እንደነበር አስታውሰው የከተማዋን መቋቋም ተከትሎ ባለፉት ሁለት ዓመታት 16 ነጥብ 5 በሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
ይህም ከከተማዋ የሚገኘው ገቢ በየጊዜው እየተሻሻለ ስለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል።
እንደ ከንቲባው ገለጻ በተያዘው ዓመት ከከተማዋ ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ባለፉት ስድስት ወራት በተደረገ እንቅስቃሴ 14 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ተችሏል።
ሸገር ከተማ የኢኮኖሚ ማዕከል እንደመሆኗ፣ ካለው የመሬት ስፋትና ከሚያስፈልገው መሰረተ ልማትና የልማት ሥራዎች አንጻር ገቢው የሚፈለገውን ያህል እንዳልሆነም ገልጸዋል።
ከተማዋ የምታመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ልማቷን ለማፋጠንና ነዋሪዎቿን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከንቲባው አስታውቀዋል።
በከተማዋ ታማኝና ግንባር ቀደም ግብር ከፋይ በመሆን ዛሬ የተሸለሙትን የንግድ ማህበረሰብ አባላት ከንቲባው አመስግነው፣ ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ በጋራ አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

በሸገር ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መልካሙ አምባው በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ከመዘጋጃ ቤታዊ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች የግብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
የግብር አሰባሰቡን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ ግብርን በወቅቱና በአግባቡ መክፈል ባለው ጠቀሜታ ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ እንዲሁም የተሻሻሉ የታክስ ህጎችን በመተግበር የተሻለ ገቢ በፍጥነት ለመሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።
በከተማው በመጀመሪያው ስድስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለውም ጠቁመዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026