የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በሸገር ከተማ 14 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰበሰበ</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት 14 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) ገለጹ።

የከተማ አስተዳደሩ ለታማኝ ግብር ከፋዮች ያዘጋጀው የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማዋ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) እንደገለጹት ዘመናዊ፤ የበለጸገና ለኑሮ ምቹ የሆነ ከተማን ለመፍጠር ዜጎች ግብራቸውን በጊዜውና በአግባቡ መክፈል ይኖርባቸዋል።


ሸገር ከተማ ከመቋቋሟ በፊት ሲሰበሰብ የነበረው ገቢ ከ6 ቢሊዮን ብር ያልበለጠ እንደነበር አስታውሰው የከተማዋን መቋቋም ተከትሎ ባለፉት ሁለት ዓመታት 16 ነጥብ 5 በሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።

ይህም ከከተማዋ የሚገኘው ገቢ በየጊዜው እየተሻሻለ ስለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል።

እንደ ከንቲባው ገለጻ በተያዘው ዓመት ከከተማዋ ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ባለፉት ስድስት ወራት በተደረገ እንቅስቃሴ 14 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ተችሏል።

ሸገር ከተማ የኢኮኖሚ ማዕከል እንደመሆኗ፣ ካለው የመሬት ስፋትና ከሚያስፈልገው መሰረተ ልማትና የልማት ሥራዎች አንጻር ገቢው የሚፈለገውን ያህል እንዳልሆነም ገልጸዋል።

ከተማዋ የምታመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ልማቷን ለማፋጠንና ነዋሪዎቿን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከንቲባው አስታውቀዋል።

በከተማዋ ታማኝና ግንባር ቀደም ግብር ከፋይ በመሆን ዛሬ የተሸለሙትን የንግድ ማህበረሰብ አባላት ከንቲባው አመስግነው፣ ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ በጋራ አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።


በሸገር ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መልካሙ አምባው በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ከመዘጋጃ ቤታዊ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች የግብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።

የግብር አሰባሰቡን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ ግብርን በወቅቱና በአግባቡ መክፈል ባለው ጠቀሜታ ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ እንዲሁም የተሻሻሉ የታክስ ህጎችን በመተግበር የተሻለ ገቢ በፍጥነት ለመሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።

በከተማው በመጀመሪያው ስድስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለውም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025