
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት 14 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) ገለጹ።
የከተማ አስተዳደሩ ለታማኝ ግብር ከፋዮች ያዘጋጀው የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማዋ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) እንደገለጹት ዘመናዊ፤ የበለጸገና ለኑሮ ምቹ የሆነ ከተማን ለመፍጠር ዜጎች ግብራቸውን በጊዜውና በአግባቡ መክፈል ይኖርባቸዋል።

ሸገር ከተማ ከመቋቋሟ በፊት ሲሰበሰብ የነበረው ገቢ ከ6 ቢሊዮን ብር ያልበለጠ እንደነበር አስታውሰው የከተማዋን መቋቋም ተከትሎ ባለፉት ሁለት ዓመታት 16 ነጥብ 5 በሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
ይህም ከከተማዋ የሚገኘው ገቢ በየጊዜው እየተሻሻለ ስለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል።
እንደ ከንቲባው ገለጻ በተያዘው ዓመት ከከተማዋ ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ባለፉት ስድስት ወራት በተደረገ እንቅስቃሴ 14 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ተችሏል።
ሸገር ከተማ የኢኮኖሚ ማዕከል እንደመሆኗ፣ ካለው የመሬት ስፋትና ከሚያስፈልገው መሰረተ ልማትና የልማት ሥራዎች አንጻር ገቢው የሚፈለገውን ያህል እንዳልሆነም ገልጸዋል።
ከተማዋ የምታመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ልማቷን ለማፋጠንና ነዋሪዎቿን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከንቲባው አስታውቀዋል።
በከተማዋ ታማኝና ግንባር ቀደም ግብር ከፋይ በመሆን ዛሬ የተሸለሙትን የንግድ ማህበረሰብ አባላት ከንቲባው አመስግነው፣ ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ በጋራ አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

በሸገር ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መልካሙ አምባው በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ከመዘጋጃ ቤታዊ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች የግብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
የግብር አሰባሰቡን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ ግብርን በወቅቱና በአግባቡ መክፈል ባለው ጠቀሜታ ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ እንዲሁም የተሻሻሉ የታክስ ህጎችን በመተግበር የተሻለ ገቢ በፍጥነት ለመሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።
በከተማው በመጀመሪያው ስድስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለውም ጠቁመዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026