የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በ3ኛው ዙር የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ግብይት ይፈፀማል ተብሎ ይጠበቃል - ሚኒስትር መላኩ አለበል</p>

Feb 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- በ3ኛው ዙር የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ግብይት ይፈፀማል ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለፁ።

3ኛው ዙር ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የ2017 ኤክስፖ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በመርሐ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የቀደምት ስልጣኔ ባለቤት ብትሆንም የምርታማነት ታሪኳ ግን አዝጋሚ ነበር።

ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ መፋጠን የአምራች ኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መጀመሩን ገልፀዋል።


ንቅናቄው ባለፉት ሁለት ዓመታት ዘርፉ አጋጥመውት የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በርካታ ስኬቶች ተገኝተዋል ብለዋል።

በተለይም የሀገር ውስጥ ተኪ ምርቶች ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት መቻሉንም አንስተዋል።

በ2017 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ብቻ ሁለት ቢሊዮን ብር የሚያወጡ ተኪ ምርቶች በሀገር ውስጥ ማምረት መቻሉን በመግለጽ።

የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፋ አጠቃላይ ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብት ዕድገት ያለው ድርሻ በየጊዜው እያደገ መምጣቱንም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።

ባለፋት ሁለት ዓመታት በተደረጉ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖዎች በፌዴራል ደረጃ ከ307 በላይ ኢንዱስትሪዎች መሳተፋቸውንና በአጠቃላይ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ግብይት መፈፀሙንም ጠቅሰዋል።


ከሚያዝያ 29 እስከ ግንቦት 5 ቀን 2017 በሚካሄደው 3ኛው ዙር የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ግብይት ይፈፀማል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።

ከሀገር ውስጥና ከውጭ በርካታ የንግድ ስምምነቶችና የገበያ ትስስሮች ይፈጠራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትሩ አንስተዋል።

መንግስት በዘርፉ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የህግ ማዕቀፎችን ከማሻሻል ባለፈ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የአምራች ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና ተወካዮች በበኩላቸው ንቅናቄው አምራችና ሸማቹን በቀላሉ በማገናኘት ለዘርፉ መነቃቃት ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ምርቶች ጥራታቸውን ጠብቀው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ በተግባር ያስመሰከረ መሆኑን አንስተዋል።

ንቅናቄው በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የነበረውን የተዛባ አመለካከት የቀየረ መሆኑንም የአምራች ኢንዱስትሪ ባለቤቶች ገልጸዋል።

3ኛው ዙር የኢትዮጵያ ታምርት የ2017 ኤክስፖ ላይ ከ200ሺህ በላይ ጎብኚዎች ይሳተፉሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026