
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- በ3ኛው ዙር የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ግብይት ይፈፀማል ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለፁ።
3ኛው ዙር ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የ2017 ኤክስፖ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በመርሐ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የቀደምት ስልጣኔ ባለቤት ብትሆንም የምርታማነት ታሪኳ ግን አዝጋሚ ነበር።
ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ መፋጠን የአምራች ኢንዱስትሪውን አቅም ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መጀመሩን ገልፀዋል።

ንቅናቄው ባለፉት ሁለት ዓመታት ዘርፉ አጋጥመውት የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በርካታ ስኬቶች ተገኝተዋል ብለዋል።
በተለይም የሀገር ውስጥ ተኪ ምርቶች ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት መቻሉንም አንስተዋል።
በ2017 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ብቻ ሁለት ቢሊዮን ብር የሚያወጡ ተኪ ምርቶች በሀገር ውስጥ ማምረት መቻሉን በመግለጽ።
የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፋ አጠቃላይ ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብት ዕድገት ያለው ድርሻ በየጊዜው እያደገ መምጣቱንም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።
ባለፋት ሁለት ዓመታት በተደረጉ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖዎች በፌዴራል ደረጃ ከ307 በላይ ኢንዱስትሪዎች መሳተፋቸውንና በአጠቃላይ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ግብይት መፈፀሙንም ጠቅሰዋል።

ከሚያዝያ 29 እስከ ግንቦት 5 ቀን 2017 በሚካሄደው 3ኛው ዙር የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ግብይት ይፈፀማል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።
ከሀገር ውስጥና ከውጭ በርካታ የንግድ ስምምነቶችና የገበያ ትስስሮች ይፈጠራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ሚኒስትሩ አንስተዋል።
መንግስት በዘርፉ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የህግ ማዕቀፎችን ከማሻሻል ባለፈ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
የአምራች ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና ተወካዮች በበኩላቸው ንቅናቄው አምራችና ሸማቹን በቀላሉ በማገናኘት ለዘርፉ መነቃቃት ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ምርቶች ጥራታቸውን ጠብቀው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ በተግባር ያስመሰከረ መሆኑን አንስተዋል።
ንቅናቄው በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የነበረውን የተዛባ አመለካከት የቀየረ መሆኑንም የአምራች ኢንዱስትሪ ባለቤቶች ገልጸዋል።
3ኛው ዙር የኢትዮጵያ ታምርት የ2017 ኤክስፖ ላይ ከ200ሺህ በላይ ጎብኚዎች ይሳተፉሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026