የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የኢትዮጵያ ፓስፖርቶች እና የጉዞ ሰነዶች ዘመኑን የዋጁ እና የተራቀቁ የደህንነት ባህሪያት እንዲኖራቸው መደረጉ ትልቅ እመርታ ነው-ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ፓስፖርቶች እና የጉዞ ሰነዶች ዘመኑን የዋጁ እና የተራቀቁ የደህንነት ባህሪያት እንዲኖራቸው መደረጉ ትልቅ እመርታ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለፁ።

ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስ ኢ-ፓስፖርት ዛሬ ይፋ ተደርጓል፡፡

በዚሁ ወቅት ፕሬዝደንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንደገለፁት፥ የኢትዮጵያ ፓስፖርቶች እና የጉዞ ሰነዶች ዘመኑን የዋጁ እና የተራቀቁ የደህንነት ባህሪያት እንዲኖራቸው መደረጉ ትልቅ እመርታ ነው።

የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት ተግባራዊ መደረጉ የሀገርን ገጽታ ከመገንባት ባሻገር ለዜጎች የተሰጠውን ዋጋ የሚገልፅ ነው ብለዋል።


ፓስፖርቱ ማንኛውንም አይነት ማጭበርበር ለመግታት የማይተካ ሚና እንደሚኖረው ፕሬዝዳንት ታዬ ተናግረዋል።

ዘመናዊ ሰነዶች የሰዎችን እንቅስቃሴ ከማፋጠን ባሻገር ንግድን ለማሳለጥና ህጋዊ የስራ ዕድል ለማግኘት አስፈላጊ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ኢ-ፓስፖርቱ ለዜጎች ጥራት እና ግልፅነት የተላበሰ አገልግሎት ለመስጠት ያግዛል ብለዋል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በበኩላቸው፥ ኢ-ፓስፖርቱ የአንድን ግለሰብ ባዮሜትሪክ መረጃ ጨምሮ የጣት አሻራዎችን፣የፊት ለይቶ ማወቂያ እና የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ ያካተተ እንደሆነ ገልፀዋል።

ኢ-ፓስፖርቱ የኢሚግሬሽን ሂደቶችን ማቀላጠፍን ጨምሮ ሀሰተኛ መረጃዎችን እና ማጭበርበርን ለመከላከል የሚያስችል የላቀ የደህንነት ባህሪያትን ያካተተ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም ሀሰተኛ ፓስፖርቶችን የመስራት ወይም የሌላ ሰው ፓስፖርትን ላልተገባ ዓላማ የመጠቀም ስጋቶችን እንደሚቀንስ አረጋግጠዋል።

ከዚህም ባሻገር የኢትዮጵያን የአየርና የየብስ ድንበሮች በአግባቡ ለመቆጣጠር እና የሀገር ደህንነትን ከመጠበቅ አኳያ ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነ አረጋግጠዋል።

ፓስፖርቱ በውስጥ ገጹ የኢትዮጵያን ቅርሶች እና ታሪካዊ ቦታዎች የሚያሳዩ ምስሎች እንዳሉትና ከዚህ ቀደም ከነበረው ፓስፖርት በቀለም እና በዲዛይን ይለያል ብለዋል።

ፓስፖርቱ በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ መመዘኛዎች ያሟላና አለም አቀፍ ተቀባይነትን ያረጋገጠ መሆኑ ነው የተገለጸው።

ኢ-ፖስፖርቱ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና በቶፓን ሴኪዩሪቲ ኢትዮጵያ አክሲዮን ማህበር አማካኝነት በሀገር ውስጥ መመረቱ በመድረኩ ላይ ተነግሯል።

በመርኃ ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምሕረት፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ፣የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025