
ሚዛን አማን፣ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፦ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሕዝባዊ ውይይት በሚዛን አማን ከተማ ተካሄዷል።

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ሊቀጠበብት ቀለመወርቅ አጥናፉ እና አቶ ሸንቃ ጋኪናንስ እንዳሉት በለውጡ መንግስት በግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ተጠቃሚ ሆነዋል።
ፓርቲው ቀረጾ የተገበራቸው ሃሳቦች የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያበስሩ እንደሆኑም ገልጸዋል።
የሚዛን አማን አየር ማረፊያን ለአብነት ጠቅሰው፤ ፕሮጀክቱ በጊዜ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ጥረቱ እንዲጠናከር አመልክተዋል።
አቶ ደምሴ ዶንታና መምህር ከድር ብርሃኑ በንጹህ መጠጥ ውሃ፣ በጤና አገልግሎት እና በመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል።
የመንግስትን የልማት ሥራዎች ስኬታማነትም የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል።

ውይይቱን የመሩት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ እንዳሉት መንግስት ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።
ትምህርትና ጤናን ጨምሮ ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የማህበራዊ ዘርፍ የልማት ስራዎችም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት።
በፓርቲው የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መሐመድ አሕመድ በበኩላቸው የተነሱ ሕዝብ ጥያቄዎችን በእቅድ ለመመለስ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026