
ሚዛን አማን፣ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፦ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሕዝባዊ ውይይት በሚዛን አማን ከተማ ተካሄዷል።

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ሊቀጠበብት ቀለመወርቅ አጥናፉ እና አቶ ሸንቃ ጋኪናንስ እንዳሉት በለውጡ መንግስት በግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ተጠቃሚ ሆነዋል።
ፓርቲው ቀረጾ የተገበራቸው ሃሳቦች የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያበስሩ እንደሆኑም ገልጸዋል።
የሚዛን አማን አየር ማረፊያን ለአብነት ጠቅሰው፤ ፕሮጀክቱ በጊዜ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ጥረቱ እንዲጠናከር አመልክተዋል።
አቶ ደምሴ ዶንታና መምህር ከድር ብርሃኑ በንጹህ መጠጥ ውሃ፣ በጤና አገልግሎት እና በመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል።
የመንግስትን የልማት ሥራዎች ስኬታማነትም የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል።

ውይይቱን የመሩት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ እንዳሉት መንግስት ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።
ትምህርትና ጤናን ጨምሮ ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የማህበራዊ ዘርፍ የልማት ስራዎችም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት።
በፓርቲው የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መሐመድ አሕመድ በበኩላቸው የተነሱ ሕዝብ ጥያቄዎችን በእቅድ ለመመለስ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026