የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ባለፉት ዓመታት በግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ ሆነናል- የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፦ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሕዝባዊ ውይይት በሚዛን አማን ከተማ ተካሄዷል።


ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ሊቀጠበብት ቀለመወርቅ አጥናፉ እና አቶ ሸንቃ ጋኪናንስ እንዳሉት በለውጡ መንግስት በግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ተጠቃሚ ሆነዋል።

ፓርቲው ቀረጾ የተገበራቸው ሃሳቦች የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያበስሩ እንደሆኑም ገልጸዋል።

የሚዛን አማን አየር ማረፊያን ለአብነት ጠቅሰው፤ ፕሮጀክቱ በጊዜ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ጥረቱ እንዲጠናከር አመልክተዋል።

አቶ ደምሴ ዶንታና መምህር ከድር ብርሃኑ በንጹህ መጠጥ ውሃ፣ በጤና አገልግሎት እና በመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል።

የመንግስትን የልማት ሥራዎች ስኬታማነትም የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል።


ውይይቱን የመሩት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ እንዳሉት መንግስት ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።

ትምህርትና ጤናን ጨምሮ ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የማህበራዊ ዘርፍ የልማት ስራዎችም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት።

በፓርቲው የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መሐመድ አሕመድ በበኩላቸው የተነሱ ሕዝብ ጥያቄዎችን በእቅድ ለመመለስ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026