
ሚዛን አማን፣ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፦ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በተቀመጡ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሕዝባዊ ውይይት በሚዛን አማን ከተማ ተካሄዷል።

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ሊቀጠበብት ቀለመወርቅ አጥናፉ እና አቶ ሸንቃ ጋኪናንስ እንዳሉት በለውጡ መንግስት በግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ተጠቃሚ ሆነዋል።
ፓርቲው ቀረጾ የተገበራቸው ሃሳቦች የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያበስሩ እንደሆኑም ገልጸዋል።
የሚዛን አማን አየር ማረፊያን ለአብነት ጠቅሰው፤ ፕሮጀክቱ በጊዜ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ጥረቱ እንዲጠናከር አመልክተዋል።
አቶ ደምሴ ዶንታና መምህር ከድር ብርሃኑ በንጹህ መጠጥ ውሃ፣ በጤና አገልግሎት እና በመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች እንዲጠናከሩ ጠይቀዋል።
የመንግስትን የልማት ሥራዎች ስኬታማነትም የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል።

ውይይቱን የመሩት በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ እንዳሉት መንግስት ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።
ትምህርትና ጤናን ጨምሮ ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የማህበራዊ ዘርፍ የልማት ስራዎችም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት።
በፓርቲው የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ መሐመድ አሕመድ በበኩላቸው የተነሱ ሕዝብ ጥያቄዎችን በእቅድ ለመመለስ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026