
ድሬዳዋ፣ የካቲት 17/2017(ኢዜአ) ፡-በድሬዳዋ የኮሪደር ልማት የስራ ባህልን ከመቀየር በዘለለ ድሬዳዋን ምቹና ተስማሚ የስራና የመኖሪያ ስፍራ የሚያደርግ መሆኑን ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።
በከንቲባ ከድር ጁሃር የተመራው የካቢኔ አባላት እየተገባደደ የሚገኘውን የ11 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት እየተመለከቱ ነው።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር በጉብኝታቸው ወቅት ከኮሪደር ልማቱ ፕሮጀክት ተቋራጮች ጋር የተወያዩ ሲሆን ልማቱን ጥራቱን ጠብቆ በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል አቅጣጫን አስቀምጠዋል።
እንደ ከንቲባ ከድር ገለፃ ቀንና ማታ እየተሰራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የድሬዳዋን የስራ ባህል በከፍተኛ ደረጃ እየለወጠው ነው።

በተጨማሪም ድሬዳዋን ፅዱና ውብ የስራና የመኖሪያ መዳረሻ እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ በልማቱ ሂደት ተቀናጅቶ መስራት ያለውን ውጤት በሌሎች ፕሮጀክቶች ለመድገም እንደተሞኮሮ ተወስዷል ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትን ሆነ ሌሎች ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተመደበለት በጀት አጠናቆ ለህብረተሰብ ለማስረከብ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ መሠረታዊ ልምድ የተቀሰመበት ወሳኝ ስራ መሆኑን በማስታወስ ።
የኮሪደር ልማቱ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች በከፍተኛ ደረጃ የሚመልስ መሆኑን ጠቅሰው በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ ዕድል አግኝተው ክህሎት እየቀሰሙ መሆናቸውን አንስተዋል።
የካቢኔ አባላቱም ቀሪ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በተቀናጀ መንገድ ዳር ለማድረስ የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026