
ድሬዳዋ፣ የካቲት 17/2017(ኢዜአ) ፡-በድሬዳዋ የኮሪደር ልማት የስራ ባህልን ከመቀየር በዘለለ ድሬዳዋን ምቹና ተስማሚ የስራና የመኖሪያ ስፍራ የሚያደርግ መሆኑን ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።
በከንቲባ ከድር ጁሃር የተመራው የካቢኔ አባላት እየተገባደደ የሚገኘውን የ11 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት እየተመለከቱ ነው።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር በጉብኝታቸው ወቅት ከኮሪደር ልማቱ ፕሮጀክት ተቋራጮች ጋር የተወያዩ ሲሆን ልማቱን ጥራቱን ጠብቆ በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል አቅጣጫን አስቀምጠዋል።
እንደ ከንቲባ ከድር ገለፃ ቀንና ማታ እየተሰራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የድሬዳዋን የስራ ባህል በከፍተኛ ደረጃ እየለወጠው ነው።

በተጨማሪም ድሬዳዋን ፅዱና ውብ የስራና የመኖሪያ መዳረሻ እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ በልማቱ ሂደት ተቀናጅቶ መስራት ያለውን ውጤት በሌሎች ፕሮጀክቶች ለመድገም እንደተሞኮሮ ተወስዷል ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትን ሆነ ሌሎች ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተመደበለት በጀት አጠናቆ ለህብረተሰብ ለማስረከብ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ መሠረታዊ ልምድ የተቀሰመበት ወሳኝ ስራ መሆኑን በማስታወስ ።
የኮሪደር ልማቱ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች በከፍተኛ ደረጃ የሚመልስ መሆኑን ጠቅሰው በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ ዕድል አግኝተው ክህሎት እየቀሰሙ መሆናቸውን አንስተዋል።
የካቢኔ አባላቱም ቀሪ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በተቀናጀ መንገድ ዳር ለማድረስ የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026