የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በድሬዳዋ እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት እየተገባደደ ነው</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ፣ የካቲት 17/2017(ኢዜአ) ፡-በድሬዳዋ የኮሪደር ልማት የስራ ባህልን ከመቀየር በዘለለ ድሬዳዋን ምቹና ተስማሚ የስራና የመኖሪያ ስፍራ የሚያደርግ መሆኑን ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።

በከንቲባ ከድር ጁሃር የተመራው የካቢኔ አባላት እየተገባደደ የሚገኘውን የ11 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት እየተመለከቱ ነው።

የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር በጉብኝታቸው ወቅት ከኮሪደር ልማቱ ፕሮጀክት ተቋራጮች ጋር የተወያዩ ሲሆን ልማቱን ጥራቱን ጠብቆ በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል አቅጣጫን አስቀምጠዋል።

እንደ ከንቲባ ከድር ገለፃ ቀንና ማታ እየተሰራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የድሬዳዋን የስራ ባህል በከፍተኛ ደረጃ እየለወጠው ነው።


በተጨማሪም ድሬዳዋን ፅዱና ውብ የስራና የመኖሪያ መዳረሻ እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ በልማቱ ሂደት ተቀናጅቶ መስራት ያለውን ውጤት በሌሎች ፕሮጀክቶች ለመድገም እንደተሞኮሮ ተወስዷል ብለዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትን ሆነ ሌሎች ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተመደበለት በጀት አጠናቆ ለህብረተሰብ ለማስረከብ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ መሠረታዊ ልምድ የተቀሰመበት ወሳኝ ስራ መሆኑን በማስታወስ ።

የኮሪደር ልማቱ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች በከፍተኛ ደረጃ የሚመልስ መሆኑን ጠቅሰው በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ ዕድል አግኝተው ክህሎት እየቀሰሙ መሆናቸውን አንስተዋል።

የካቢኔ አባላቱም ቀሪ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በተቀናጀ መንገድ ዳር ለማድረስ የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026