
ድሬዳዋ፣ የካቲት 17/2017(ኢዜአ) ፡-በድሬዳዋ የኮሪደር ልማት የስራ ባህልን ከመቀየር በዘለለ ድሬዳዋን ምቹና ተስማሚ የስራና የመኖሪያ ስፍራ የሚያደርግ መሆኑን ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።
በከንቲባ ከድር ጁሃር የተመራው የካቢኔ አባላት እየተገባደደ የሚገኘውን የ11 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት እየተመለከቱ ነው።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር በጉብኝታቸው ወቅት ከኮሪደር ልማቱ ፕሮጀክት ተቋራጮች ጋር የተወያዩ ሲሆን ልማቱን ጥራቱን ጠብቆ በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል አቅጣጫን አስቀምጠዋል።
እንደ ከንቲባ ከድር ገለፃ ቀንና ማታ እየተሰራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የድሬዳዋን የስራ ባህል በከፍተኛ ደረጃ እየለወጠው ነው።

በተጨማሪም ድሬዳዋን ፅዱና ውብ የስራና የመኖሪያ መዳረሻ እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ በልማቱ ሂደት ተቀናጅቶ መስራት ያለውን ውጤት በሌሎች ፕሮጀክቶች ለመድገም እንደተሞኮሮ ተወስዷል ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትን ሆነ ሌሎች ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተመደበለት በጀት አጠናቆ ለህብረተሰብ ለማስረከብ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ መሠረታዊ ልምድ የተቀሰመበት ወሳኝ ስራ መሆኑን በማስታወስ ።
የኮሪደር ልማቱ የነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች በከፍተኛ ደረጃ የሚመልስ መሆኑን ጠቅሰው በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ ዕድል አግኝተው ክህሎት እየቀሰሙ መሆናቸውን አንስተዋል።
የካቢኔ አባላቱም ቀሪ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በተቀናጀ መንገድ ዳር ለማድረስ የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026