የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በወልቂጤ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረጉ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፡- በወልቂጤ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ።

በብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ህዝባዊ ኮንፍረንስ ዛሬ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ የተሳተፉ የወልቂጤ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች መልካም መሆናቸውን አንስተው ተጠናከረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወይዘሮ መሰረት ተሟሪ እና ወጣት ዳውድ ካሚል፤ በወልቂጤ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን አንስተዋል።


በጉራጌ ዞን በገጠር ኮሪደር ልማት የተሰራውን ሥራ በአርአያነት ጠቅሰው በወልቂጤ ከተማም ልማቱ በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርበታል ነው ያሉት።

በከተማዋ የሚስተዋለው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታትም ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።


ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ሙንተሃ ኢብራሂምና አቶ አቡ ገበየሁ፤ የተለያዩ የልማት ስራዎች በጥራትና በፍጥነት በመንግስትና በህዝብ ትብብር እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በጥሩ ክንውን ላይ ያሉትን በማድነቅ በተለይም የዋቤ የኤሌክትሪክ ግድብ ፕሮጀክትና የወልቂጤ ጠቅላላ ሆስፒታል ግንባታ ሥራ በአፋጣኝ ተጠናቆ ለአገልገሎት እንዲበቃ ጠይቀዋል።


የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ፤ ህብረተሰቡ የመንግስትን ጥረት በማገዝ የልማት አጋርነቱን በተግባር እያሳየ መሆኑን ገልጸው በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ረዳት ተጠሪ ይሁን አሰፋ፤ በሁሉም አካባቢዎች የልማት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠልና ሰላምን በዘላቂነት ማስጠበቅ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል።


የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ፤ በየደረጃው ያለው አመራር ህዝብን በቅንነት፣ በታማኝነትና በውጤታማነት ለማገልገል ዝግጁ መሆን እንዳለበት አሳስበው የህዝቡ ትብብር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።


በፓርቲም ይሁን በመንግስት ደረጃ ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት የተሟላ ዝግጁነት ስለመኖሩም አረጋግጠዋል።

የዋቤ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ሜጋ ፕሮጀክት ለመስኖ እና ለቱሪዝም ዘርፍ ጭምር አስተዋጽኦ እንዲኖረው ታሳቢ ተደርጎ እንዲለማ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ይሰራል ሲሉም አክለዋል።

የወልቂጤ ከተማን ማስተር ፕላን ለማስጠበቅ የህዝቡ ትብብርና ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ በኮንፍረንሱ ከነዋሪዎች የተነሱ ሃሳቦች በቀጣይ ለተሻለ ሥራ ለመዘጋጀት አጋዥ መሆናቸውን አስረድተዋል።

በህዝባዊ ኮንፍረንሱ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራር አካላት እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍል ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026