የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በወልቂጤ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረጉ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፡- በወልቂጤ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብን ተጠቃሚነት መሰረት ያደረጉ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ።

በብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ህዝባዊ ኮንፍረንስ ዛሬ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ የተሳተፉ የወልቂጤ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች መልካም መሆናቸውን አንስተው ተጠናከረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወይዘሮ መሰረት ተሟሪ እና ወጣት ዳውድ ካሚል፤ በወልቂጤ ከተማና አካባቢው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ታሳቢ ያደረጉ መሆናቸውን አንስተዋል።


በጉራጌ ዞን በገጠር ኮሪደር ልማት የተሰራውን ሥራ በአርአያነት ጠቅሰው በወልቂጤ ከተማም ልማቱ በተጠናከረ መልኩ መቀጠል ይኖርበታል ነው ያሉት።

በከተማዋ የሚስተዋለው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታትም ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።


ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ሙንተሃ ኢብራሂምና አቶ አቡ ገበየሁ፤ የተለያዩ የልማት ስራዎች በጥራትና በፍጥነት በመንግስትና በህዝብ ትብብር እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በጥሩ ክንውን ላይ ያሉትን በማድነቅ በተለይም የዋቤ የኤሌክትሪክ ግድብ ፕሮጀክትና የወልቂጤ ጠቅላላ ሆስፒታል ግንባታ ሥራ በአፋጣኝ ተጠናቆ ለአገልገሎት እንዲበቃ ጠይቀዋል።


የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላጫ ጋሩማ፤ ህብረተሰቡ የመንግስትን ጥረት በማገዝ የልማት አጋርነቱን በተግባር እያሳየ መሆኑን ገልጸው በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ረዳት ተጠሪ ይሁን አሰፋ፤ በሁሉም አካባቢዎች የልማት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠልና ሰላምን በዘላቂነት ማስጠበቅ የጋራ አጀንዳችን ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል።


የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ፤ በየደረጃው ያለው አመራር ህዝብን በቅንነት፣ በታማኝነትና በውጤታማነት ለማገልገል ዝግጁ መሆን እንዳለበት አሳስበው የህዝቡ ትብብር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።


በፓርቲም ይሁን በመንግስት ደረጃ ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት የተሟላ ዝግጁነት ስለመኖሩም አረጋግጠዋል።

የዋቤ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ሜጋ ፕሮጀክት ለመስኖ እና ለቱሪዝም ዘርፍ ጭምር አስተዋጽኦ እንዲኖረው ታሳቢ ተደርጎ እንዲለማ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ይሰራል ሲሉም አክለዋል።

የወልቂጤ ከተማን ማስተር ፕላን ለማስጠበቅ የህዝቡ ትብብርና ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ በኮንፍረንሱ ከነዋሪዎች የተነሱ ሃሳቦች በቀጣይ ለተሻለ ሥራ ለመዘጋጀት አጋዥ መሆናቸውን አስረድተዋል።

በህዝባዊ ኮንፍረንሱ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራር አካላት እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍል ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026