
አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናን በመሠረተ-ልማት ለማስተሳሰር በሚደረገው ጥረት ውስጥ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ ግዛቸው አስራት (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለጎሮቤት ሀገራት ቅድሚያ የሚሰጥ በጋራ መልማት፣ ማደግና መበልጸግን ጨምሮ የጋራ ደህንነትን በትብብር ማስጠበቅን መሠረት ያደረገ ነው፡፡
ለጎሮቤት ሀገራት ሰላምና እድገት ቅድሚያ የሚሰጥ፣ ከሌሎች ሀገራት ጋር አብሮ የመልማትና የማደግ መርህ ላይ የተመሰረተ ዲፕሎማሲያዊ አቅጣጫም እንዳለው ይታወቃል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን ለመዋጋትና ለመከላከል እየወሰደች ያለው ቁርጠኝነት ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ ግዛቸው አስራት(ዶ/ር) እንዳሉት፤ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ከፍተኛ አምራች ዜጋ ያለበት፣ በተፈጥሮ ሃብት የበለጸገ እንዲሁም ስብጥር ያለው ማህበረሰብ የሚኖርበት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ቀጣናውን በመሠረተ ልማት ለማስተሳሰር እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች መሆኗን ጠቁመው፤ ቀጣናውን በመንገድና በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ለማስተሳሰር እየተደረገ ያለውን ጥረት ለአብነት አንስተዋል።
የቀጣናው ሀገራት እንደ ድርቅና ሽብርተኝነት ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ያሉ የጋራ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ማጎልበት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026