አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናን በመሠረተ-ልማት ለማስተሳሰር በሚደረገው ጥረት ውስጥ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ ግዛቸው አስራት (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለጎሮቤት ሀገራት ቅድሚያ የሚሰጥ በጋራ መልማት፣ ማደግና መበልጸግን ጨምሮ የጋራ ደህንነትን በትብብር ማስጠበቅን መሠረት ያደረገ ነው፡፡
ለጎሮቤት ሀገራት ሰላምና እድገት ቅድሚያ የሚሰጥ፣ ከሌሎች ሀገራት ጋር አብሮ የመልማትና የማደግ መርህ ላይ የተመሰረተ ዲፕሎማሲያዊ አቅጣጫም እንዳለው ይታወቃል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ በቀጣናው ሽብርተኝነትን ለመዋጋትና ለመከላከል እየወሰደች ያለው ቁርጠኝነት ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ ግዛቸው አስራት(ዶ/ር) እንዳሉት፤ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ከፍተኛ አምራች ዜጋ ያለበት፣ በተፈጥሮ ሃብት የበለጸገ እንዲሁም ስብጥር ያለው ማህበረሰብ የሚኖርበት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ቀጣናውን በመሠረተ ልማት ለማስተሳሰር እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ ግንባር ቀደም ሚናዋን እየተወጣች መሆኗን ጠቁመው፤ ቀጣናውን በመንገድና በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ለማስተሳሰር እየተደረገ ያለውን ጥረት ለአብነት አንስተዋል።
የቀጣናው ሀገራት እንደ ድርቅና ሽብርተኝነት ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ያሉ የጋራ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ማጎልበት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025