አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የቻይና ጃንግዙ ግዛት ባለሀብቶች ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በኢትዮጵያ መዋለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በጃንግዙ ግዛት የንግድ ቢሮ ዳይሬክተር ጄነራል ሲ ዮንግ ከተመራ የቢዝነስ ልዑክ ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
የቻይና ባለሀብቶች የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም የፈጠረውን ምቹ ከባቢ በመጠቀም መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
የጆንግዙ ግዛት ንግድ ቢሮ ዳይሬክተር ጄነራል ሲ ዮንግ ኢትዮጵያ እና ቻይና ጠንካራ የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
የግዛቷ ባለሀብቶች በተለይ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው እና ቢሮው ይህንኑ ወደ ተግባር ለመቀየር የሚያስችል ስምምነት ለማድረግም ዝግጁ መሆኑን አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ ከሶስት ሺህ በላይ የቻይና ድርጅቶች በኢንቨስትመንት ተሰማርተው እንደሚገኙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025