የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የቻይና ጃንግዙ ግዛት ባለሀብቶች በኢትዮጵያ መዋለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የቻይና ጃንግዙ ግዛት ባለሀብቶች ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በኢትዮጵያ መዋለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በጃንግዙ ግዛት የንግድ ቢሮ ዳይሬክተር ጄነራል ሲ ዮንግ ከተመራ የቢዝነስ ልዑክ ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።

የቻይና ባለሀብቶች የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም የፈጠረውን ምቹ ከባቢ በመጠቀም መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።

የጆንግዙ ግዛት ንግድ ቢሮ ዳይሬክተር ጄነራል ሲ ዮንግ ኢትዮጵያ እና ቻይና ጠንካራ የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸዋል።

የግዛቷ ባለሀብቶች በተለይ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው እና ቢሮው ይህንኑ ወደ ተግባር ለመቀየር የሚያስችል ስምምነት ለማድረግም ዝግጁ መሆኑን አመልክተዋል።

በኢትዮጵያ ከሶስት ሺህ በላይ የቻይና ድርጅቶች በኢንቨስትመንት ተሰማርተው እንደሚገኙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025