
አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የቻይና ጃንግዙ ግዛት ባለሀብቶች ማኑፋክቸሪንግን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች በኢትዮጵያ መዋለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በጃንግዙ ግዛት የንግድ ቢሮ ዳይሬክተር ጄነራል ሲ ዮንግ ከተመራ የቢዝነስ ልዑክ ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
የቻይና ባለሀብቶች የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም የፈጠረውን ምቹ ከባቢ በመጠቀም መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
የጆንግዙ ግዛት ንግድ ቢሮ ዳይሬክተር ጄነራል ሲ ዮንግ ኢትዮጵያ እና ቻይና ጠንካራ የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
የግዛቷ ባለሀብቶች በተለይ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው እና ቢሮው ይህንኑ ወደ ተግባር ለመቀየር የሚያስችል ስምምነት ለማድረግም ዝግጁ መሆኑን አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ ከሶስት ሺህ በላይ የቻይና ድርጅቶች በኢንቨስትመንት ተሰማርተው እንደሚገኙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026