የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የኢትዮጵያና ቻይናን የኢኮኖሚና ንግድ ትብብር የሚያጠናክር ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያና ቻይና መካከል ያለውን የኢኮኖሚና ንግድ ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በኮንፍረንሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምሥራቅ፣ ኤስያ እና ፓስፊክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ንጉሥ ከበደ፣ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሀይ፣ የጃንግዙ ግዛት የንግድ መምሪያ ዋና ዳይሬክተር ሲ ዮንግና የግዛቲቱ ባለሃብቶች ተሳትፈዋል።

አምባሳደር ንጉሥ ከበደ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፤ የኢትዮጵያና ቻይና የኢኮኖሚና ንግድ ትብብር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ነው።

ይህም ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን እያደረገች ያለው ጉዞ እውን እንዲሆን የሚያግዝ ነው ብለዋል።


የቻይናዋ ጃንግዙ ግዛት በዚህ የትብብር ሂደት አይተኬ ሚና እንዳላት ገልፀዋል።

የግዛቲቱ ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ ኢንቨስት በማድረግ የኢኮኖሚና የንግድ ትብብርን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሀይ በበኩላቸው ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠሉን አረጋግጠዋል።

የኢትዮ-ቻይና በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ስትራቴጂክ አጋርነት በኢኮኖሚና ንግድ የበለጠ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።

የቻይና ጃንግዙ ግዛት የንግድ መምሪያ ዋና ዳይሬክተር ሲ ዮንግ ኢትዮጵያ ለግዛቲቱ ባለሃብቶች ምቹ የኢኮኖሚና የንግድ መዳረሻ እንደሆነች ተናግረዋል።

በተለይ የግዛቲቷ ባለሀብቶች በማኑፋክቸሪንግ፣ በታዳሽ ኃይል፣ በዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ የሚያደርጉትን ተሳትፎ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026