አዲስ አበባ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የሩዝ ሰብል የሚለማን የመሬት ሽፋን ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መድረሱን የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ እንዳሉት ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት ራስ በቅ ለመሆን በሰጠችው ትኩረት አሁን ላይ በስንዴ ምርት ራሷን ችላለች።
በስንዴ ምርት የተገኘውን ስኬት ደግሞ እስከ 2018 ዓ.ም በሩዝ ምርት ለመድገም በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በሩዝ ሰብል የሚለማ መሬት ሽፋን ከነበረበት ከ200 እስከ 300 ሺህ ሄክታር ወደ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
የሩዝ ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ መጠን መጨመሩን ጠቅሰው፤ ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ ከጃፓን መንግስት ጋር በትብብር እየተሰራ ስለመሆኑ አንስተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025