
ሀዋሳ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለስኬት እንዲበቁ የምክር ቤቱ የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ።
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ በማካሄድ ላይ ሲሆን የአስፈፃሚውን የስድስት ወራት አፈፃፀም መገምገም ጀምሯል።
የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ፤ ሁሉም አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በሚያደርጓቸው ጥረቶች የምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ ያልተለየ መሆኑን ገልጸዋል።

በግብርናው ዘርፍ በበጋ መስኖ ልማት በማህበር የተደራጁ ዜጎችን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ ባደረግነው ምልከታ አረጋግጠናል ብለዋል።
በሌማት ትሩፋት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በሌሎች የግብርና፣ የኢንዱስትሪና የቱሪዝም ዘርፎች በክልሉ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ተስፋ ያላቸው መሆናቸውንም አፈ ጉባኤዋ አንስተዋል።
በመሆኑም በክልሉ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለስኬት እንዲበቁ የምክር ቤቱ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።
በሁሉም ዘርፎች የተያዙ ዕቅዶች መሬት ወርደው የህዝብን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ የምክር ቤት አባላት የሚያደርጉ ክትትልና ቁጥጥር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት የተሻለ አፈጻጸም ያላቸውን ተቋማት ለይቶ ለማበረታታት የሚያስችል አሰራር ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
ጉባዔው ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን የተለያዩ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ሹመቶችንም ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026