የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በክልሉ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለስኬት እንዲበቁ የምክር ቤቱ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለስኬት እንዲበቁ የምክር ቤቱ የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ።

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ በማካሄድ ላይ ሲሆን የአስፈፃሚውን የስድስት ወራት አፈፃፀም መገምገም ጀምሯል።

የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ፤ ሁሉም አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በሚያደርጓቸው ጥረቶች የምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ ያልተለየ መሆኑን ገልጸዋል።

በግብርናው ዘርፍ በበጋ መስኖ ልማት በማህበር የተደራጁ ዜጎችን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ ባደረግነው ምልከታ አረጋግጠናል ብለዋል።

በሌማት ትሩፋት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በሌሎች የግብርና፣ የኢንዱስትሪና የቱሪዝም ዘርፎች በክልሉ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ተስፋ ያላቸው መሆናቸውንም አፈ ጉባኤዋ አንስተዋል።

በመሆኑም በክልሉ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለስኬት እንዲበቁ የምክር ቤቱ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።

በሁሉም ዘርፎች የተያዙ ዕቅዶች መሬት ወርደው የህዝብን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ የምክር ቤት አባላት የሚያደርጉ ክትትልና ቁጥጥር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት የተሻለ አፈጻጸም ያላቸውን ተቋማት ለይቶ ለማበረታታት የሚያስችል አሰራር ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

ጉባዔው ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን የተለያዩ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ሹመቶችንም ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026