የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በክልሉ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለስኬት እንዲበቁ የምክር ቤቱ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለስኬት እንዲበቁ የምክር ቤቱ የድጋፍና ክትትል ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ ገለጹ።

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ በማካሄድ ላይ ሲሆን የአስፈፃሚውን የስድስት ወራት አፈፃፀም መገምገም ጀምሯል።

የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ፤ ሁሉም አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በሚያደርጓቸው ጥረቶች የምክር ቤቱ ክትትልና ድጋፍ ያልተለየ መሆኑን ገልጸዋል።

በግብርናው ዘርፍ በበጋ መስኖ ልማት በማህበር የተደራጁ ዜጎችን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ ባደረግነው ምልከታ አረጋግጠናል ብለዋል።

በሌማት ትሩፋት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በሌሎች የግብርና፣ የኢንዱስትሪና የቱሪዝም ዘርፎች በክልሉ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ተስፋ ያላቸው መሆናቸውንም አፈ ጉባኤዋ አንስተዋል።

በመሆኑም በክልሉ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት ለስኬት እንዲበቁ የምክር ቤቱ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።

በሁሉም ዘርፎች የተያዙ ዕቅዶች መሬት ወርደው የህዝብን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ የምክር ቤት አባላት የሚያደርጉ ክትትልና ቁጥጥር በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት የተሻለ አፈጻጸም ያላቸውን ተቋማት ለይቶ ለማበረታታት የሚያስችል አሰራር ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

ጉባዔው ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን የተለያዩ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ሹመቶችንም ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026