
ሰቆጣ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረገው ጥረት የፍራፍሬ ልማቱ ውጤት እየታየበት መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ የዋግ ኽምራ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳግም ባይነሳኝ ገለጹ።
የብልፅግና ፓርቲ የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የስድስት ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በዝቋላ ወረዳ አካሂዷል።
የብልፅግና ፓርቲ የዋግ ኽምራ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳግም ባይነሳኝ በግምገማው ላይ እንዳሉት በብሔረሰብ አስተዳደሩ በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረገው ጥረት የውሃ አማራጭን በመጠቀም የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሮችን አኗኗር እየቀየሩ መጥተዋል።

በተለይም የዝቋላ አርሶ አደሮች የአካባቢን ስነ ምህዳር መሰረት ያደረጉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን በማልማት ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።
የልማት ተሞክሮውን በዞኑ ለማስፋት በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።
በአስተዳደሩ የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በበኩላቸው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከአዝርእት ልማት ጎን ለጎን ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በትኩረት እየተሰራ ነው።
በዞኑም በዘንድሮው ዓመት በመስኖ ከሚለማው 4ሺህ 524 ሄክታር መሬት ውስጥ 373 ሄክታሩ በቋሚ ፍራፍሬና አትክልት እየለማ መሆኑን ገልፀዋል።
በቆላማ ወረዳዎች በክላስተር የአትክልት ልማትን ለማስፋፋት 18ሺህ አርሶ አደሮች በቋሚ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ላይ ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዝቋላ ወረዳ የፅፅቃ ከተማ ነዋሪ ቄስ ሙሉዓለም በላይ በበኩላቸው የፅፅቃ ወንዝን በመጠቀም አንድ ሄክታር ማሳቸው ላይ ማንጎ፣ ሎሚ፣ ቡና፣ ጌሾና ሌሎች ቋሚ አትክልቶችን እያለሙ ይገኛሉ።
የፍራፍሬ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ መሬታቸው ጪንጫ በመሆኑ ከሌላ አካባቢ አፈር አምጥተው በመደልደል መስራታቸውን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ከተረጂነት ለመላቀቅ ብቸኛው አማራጭ ተግቶ መስራት ነው ያሉት ቄስ ሙሉዓለም ወጣቱ ከእርሳቸው ተሞክሮ በመውሰድ የአካባቢውን ፀጋ በማልማት ተጠቃሚነቱን እንዲያረጋግጥም መክረዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026