አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡- የሳይበር ደህንነትን የማስጠበቅ ሀገራዊ አቅም እያደገ መምጣቱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ተናገሩ።
ዋና ዳይሬክተሯ በተቋሙ የሪፎርም ስራዎች፣ እየተገኙ ባሉ ውጤቶና ቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅና የመከላከል አቅምን ማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
ከለውጥ ስራዎቹ መካከል የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ ስራ ላይ መዋሉን አስታውሰዋል።
ኮምፒውተርን በመጠቀም የሚፈጸሙ ወንጀሎችን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችል አዋጅ መውጣቱን ጠቅሰው፣ ይህም ወንጀልን የመከላከል ሀገራዊ አቅምን ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
ከውጭ የሚገቡ ቴክኖሎጂዎችን ከደህንነት አኳያ በአግባቡ ተፈትሸው ወደ ሀገር እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑንም ነው ያብራሩት።
ከቁልፍ መሰረተ ልማት ተቋማት ጥበቃ ጋር በተያያዘ አስቀድሞ የመከላከል ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ተቋማት የሳይበር ጥቃቶችን መከላከል የሚችሉበት አቅም እንዲገነቡ ስልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም የተሻለ የአሰራር ስርዓት እንዲኖራቸው አስተዳደሩ ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል።
የማህበረሰቡን ንቃተ ህሊና ማሳደግ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል ቁልፍ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ እንደመሆኑ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
በዘርፉ የሰው ሃይልን ለማፍራት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፣ ለአብነትም ከተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ ታዳጊዎች በክረምት መርሃ ግብር እንዲሰለጥኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በሳይበር ደህንነት ላይ ትኩረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ደረጃ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት እየተሠራ ነው ብለዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025