የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የሳይበር ደህንነትን የማስጠበቅ ሀገራዊ አቅም እያደገ መጥቷል - የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፡- የሳይበር ደህንነትን የማስጠበቅ ሀገራዊ አቅም እያደገ መምጣቱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ተናገሩ።

ዋና ዳይሬክተሯ በተቋሙ የሪፎርም ስራዎች፣ እየተገኙ ባሉ ውጤቶና ቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅና የመከላከል አቅምን ማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።

ከለውጥ ስራዎቹ መካከል የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ ስራ ላይ መዋሉን አስታውሰዋል።

ኮምፒውተርን በመጠቀም የሚፈጸሙ ወንጀሎችን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችል አዋጅ መውጣቱን ጠቅሰው፣ ይህም ወንጀልን የመከላከል ሀገራዊ አቅምን ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

ከውጭ የሚገቡ ቴክኖሎጂዎችን ከደህንነት አኳያ በአግባቡ ተፈትሸው ወደ ሀገር እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑንም ነው ያብራሩት።

ከቁልፍ መሰረተ ልማት ተቋማት ጥበቃ ጋር በተያያዘ አስቀድሞ የመከላከል ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

ተቋማት የሳይበር ጥቃቶችን መከላከል የሚችሉበት አቅም እንዲገነቡ ስልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም የተሻለ የአሰራር ስርዓት እንዲኖራቸው አስተዳደሩ ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል።

የማህበረሰቡን ንቃተ ህሊና ማሳደግ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል ቁልፍ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ እንደመሆኑ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

በዘርፉ የሰው ሃይልን ለማፍራት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፣ ለአብነትም ከተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ ታዳጊዎች በክረምት መርሃ ግብር እንዲሰለጥኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በሳይበር ደህንነት ላይ ትኩረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ደረጃ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት እየተሠራ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025