
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የኤሌክትሮኒክ ግዢ ስርዓት ተግባራዊ መደረጉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ እንዳስቻላቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ገለፁ።
የፌደራል የመንግስት ግዢ አገልግሎት የፌደራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የበጀት ዓመቱን የስድስት ወራት አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ገምግሟል።

የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ድሪባ ኢቲቻ(ዶ/ር) እንዳሉት ኤሌክትሮኒክ ስርዓት መተግበሩ ግልፅነት እና ተጠያቂነትን በመፍጠር ለአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል።
በዚህም ዩኒቨርሲቲው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን በወቅቱ ተልዕኮውን በውጤታማነት እንዲወጣ እያገዘ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ታድዮስ ሜንታ(ዶ/ር) በበኩላቸው የግዢ ስርዓት ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ወጪ ቆጣቢና ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን ነው የጠቀሱት።

በዚህም ስራዎች በተያዘላቸው እቅድ መሰረት ለማከናወን በከፍተኛ ደረጃ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።
የፌደራል የመንግስት ግዢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ አስማረ ይገዙ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት ለፌደራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በኤሌክትሮኒክ ግዢ (e-GP) መፈጸሙን ተናግረዋል።

በግማሽ አመቱ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድም ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስገኘቱን ነው የተናገሩት።
የቴክኖሎጂ ግብዓትን በማሟላትና የአቅም ግንባታ ስራ በመሰራቱ የማዕቀፍ ስምምነትና ስትራቴጂያዊ ግዢዎችን ሙሉ በሙሉ በመንግስት የኤሌክትሮኒክ ግዢ ስርዓት ተፈጻሚ እንዲሆኑ መደረጉን ጨምረው ገልጸዋል።
ከተቋሙ የሪፎርም ስራዎች መካከል የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራ ዋነኛው ሲሆን ለውጤታማነቱ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል።
ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሲስተም መቆራረጥ ጋር ተያይዞ ከተገልጋዮች ሲነሱ የነበሩ ቅሬታዎች በአሁኑ ወቅት እንዲቀረፉ መደረጉን ጠቅሰዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026