የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የኤሌክትሮኒክ ግዢ ስርዓት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት አስገኝቷል- ዩኒቨርሲቲዎች</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የኤሌክትሮኒክ ግዢ ስርዓት ተግባራዊ መደረጉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ እንዳስቻላቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ገለፁ።

የፌደራል የመንግስት ግዢ አገልግሎት የፌደራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የበጀት ዓመቱን የስድስት ወራት አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ገምግሟል።


የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ድሪባ ኢቲቻ(ዶ/ር) እንዳሉት ኤሌክትሮኒክ ስርዓት መተግበሩ ግልፅነት እና ተጠያቂነትን በመፍጠር ለአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል።

በዚህም ዩኒቨርሲቲው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን በወቅቱ ተልዕኮውን በውጤታማነት እንዲወጣ እያገዘ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ታድዮስ ሜንታ(ዶ/ር) በበኩላቸው የግዢ ስርዓት ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ወጪ ቆጣቢና ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን ነው የጠቀሱት።


በዚህም ስራዎች በተያዘላቸው እቅድ መሰረት ለማከናወን በከፍተኛ ደረጃ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።

የፌደራል የመንግስት ግዢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ አስማረ ይገዙ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት ለፌደራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በኤሌክትሮኒክ ግዢ (e-GP) መፈጸሙን ተናግረዋል።


በግማሽ አመቱ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድም ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስገኘቱን ነው የተናገሩት።

የቴክኖሎጂ ግብዓትን በማሟላትና የአቅም ግንባታ ስራ በመሰራቱ የማዕቀፍ ስምምነትና ስትራቴጂያዊ ግዢዎችን ሙሉ በሙሉ በመንግስት የኤሌክትሮኒክ ግዢ ስርዓት ተፈጻሚ እንዲሆኑ መደረጉን ጨምረው ገልጸዋል።

ከተቋሙ የሪፎርም ስራዎች መካከል የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራ ዋነኛው ሲሆን ለውጤታማነቱ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል።

ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሲስተም መቆራረጥ ጋር ተያይዞ ከተገልጋዮች ሲነሱ የነበሩ ቅሬታዎች በአሁኑ ወቅት እንዲቀረፉ መደረጉን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026