
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የኤሌክትሮኒክ ግዢ ስርዓት ተግባራዊ መደረጉ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ እንዳስቻላቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ገለፁ።
የፌደራል የመንግስት ግዢ አገልግሎት የፌደራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የበጀት ዓመቱን የስድስት ወራት አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ገምግሟል።

የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ድሪባ ኢቲቻ(ዶ/ር) እንዳሉት ኤሌክትሮኒክ ስርዓት መተግበሩ ግልፅነት እና ተጠያቂነትን በመፍጠር ለአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል።
በዚህም ዩኒቨርሲቲው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን በወቅቱ ተልዕኮውን በውጤታማነት እንዲወጣ እያገዘ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ታድዮስ ሜንታ(ዶ/ር) በበኩላቸው የግዢ ስርዓት ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ወጪ ቆጣቢና ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት ማስቻሉን ነው የጠቀሱት።

በዚህም ስራዎች በተያዘላቸው እቅድ መሰረት ለማከናወን በከፍተኛ ደረጃ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።
የፌደራል የመንግስት ግዢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ አስማረ ይገዙ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት ለፌደራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በኤሌክትሮኒክ ግዢ (e-GP) መፈጸሙን ተናግረዋል።

በግማሽ አመቱ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድም ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስገኘቱን ነው የተናገሩት።
የቴክኖሎጂ ግብዓትን በማሟላትና የአቅም ግንባታ ስራ በመሰራቱ የማዕቀፍ ስምምነትና ስትራቴጂያዊ ግዢዎችን ሙሉ በሙሉ በመንግስት የኤሌክትሮኒክ ግዢ ስርዓት ተፈጻሚ እንዲሆኑ መደረጉን ጨምረው ገልጸዋል።
ከተቋሙ የሪፎርም ስራዎች መካከል የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራ ዋነኛው ሲሆን ለውጤታማነቱ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል።
ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሲስተም መቆራረጥ ጋር ተያይዞ ከተገልጋዮች ሲነሱ የነበሩ ቅሬታዎች በአሁኑ ወቅት እንዲቀረፉ መደረጉን ጠቅሰዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026