
ሀዋሳ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፡-የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ጉባኤ ከ4 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት፣ የተለያዩ ሹመቶችና አንድ አዋጅ በማጽደቅ ተጠናቀቀ።
ምክር ቤቱ ዛሬ ሹመት የሰጠው ለሁለት የቢሮ ሃላፊዎችና ለ46 ዳኞች መሆኑም ተመላክቷል።
ምክር ቤቱ ለክልሉ የልማት ሥራዎች ማስፈጸሚያ ከፌዴራል መንግስትና ከክልሉ መንግስት ገቢ በአጠቃላይ 4 ቢሊዮን 674 ሚሊዮን 134 ሺህ ብር በጀት አጽድቋል።
ከበጀቱ ውስጥ ከ2 ቢሊዮን 842 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆነው ከፌዴራል መንግሥት የተገኘ ሲሆን ቀሪው ከክልሉ መንግሥት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢዎች የተገኘ መሆኑ ተገልጿል።

ምክር ቤቱ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ አቅራቢነት ሹመት የሰጠው ለክልሉ ፋይናንስ ቢሮ እና ለገቢዎች ቢሮ ሥራ ሀላፊዎች ነው።

በዚህም አቶ ሀይሌ አርሲሳ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ሀላፊ እንዲሁም አቶ ደምሴ እሳቱ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ በመሆን ተሹመዋል።
በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቅራቢነት በክልሉ ለሚገኙ የመጀመሪያ ደረጃና ከፍተኛ ፍርድ ቤቶችም 46 ዳኞችን ምክር ቤቱ ዛሬ ሹመት ሰጥቷል።

ለዳኝነት ሹመት ከተሰጣቸውም አራቱ ሴቶች ናቸው።
ዳኞቹ ለህብረተሰቡ ትክክለኛና ሚዛናዊ ፍትህ በመስጠት በታማኝነትና በቅንነት እንዲያገለግሉ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ደምሴ ዱለቻ አሳስበዋል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ ሁለት ዳኞችን በስነምግባር ጥሰት ምክንያት ከሃላፊነታቸው ያሰናበተ መሆኑን ገልጸው፣ ሌሎች 34 ዳኞች እያንዳንዳቸው የሦስት ወር ደመወዝ መቀጣታቸውን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ምክር ቤቱ ከሀላፊነት የተነሱ አስፈጻሚ አካላት፣ የህዝብ ተመራጮች እና የዳኝነት አካላት መብትና ጥቅማ ጥቅሞችን ለመወሰን የወጣ አዋጅና አንድ ደንብ በማጽደቅ ተጠናቋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026