
አዳማ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተገነባ ያለው የምርምርና ቴክኖሎጂ ፓርክ የምርምር ሥርፀትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን እንደሚያፋጥን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።
ዩኒቨርሲቲው ያስገነባቸውን የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ዛሬ አስመርቋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትርና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ዛሬ በዩኒቨርሲቲው ለምረቃ የበቁት ፕሮጀክቶች ለመማር ማስተማር ስራው አዎንታዊ ሚና አላቸው።
በተለይ በዩኒቨርሲቲው እየተገነቡ ያሉ የምርምርና የቴክኖሎጂ ፓርክና ዳታ ሴንተር የምርምር ሥርፀትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያፋጥኑ ናቸው ብለዋል።
እንደ ሀገር ኢንዱስትሪውን በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ፣ አዳዲስ የአመራረት ሂደትን ለመከተልና ቴክኖሎጂን ለማላመድ ወሳኝ መሆናቸውንም ነው ሚኒስትሩ የጠቆሙት።

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው እንዳሉት ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን ማስተዳደር እንዲችሉና ራስ ገዝ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው።
ለዚህም አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለገቢ ማመንጫነት አስገንብቶ ዛሬ ካስመረቃቸው ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነውን የቢዝነስ ሴንተር በማሳያነት ጠቅሰዋል።
ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠርና የመምህራን መኖሪያ ቤት ችግርን መፍታት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለውም አቶ ኮራ አስገንዘበዋል።
በተለይ የህፃናት ማቆያ በተደራጀ መልኩ ተገንብቶ ለአገልግሎት መብቃቱ ሠራተኞች ሳይቸገሩ ልጆቻቸውን ለማሳደግ ያስችላቸዋል ብለዋል።
አቶ ኮራ እንዳሉት በአዳማ ዩኒቨርሲቲ በግንባታ ላይ ያለው የምርምር ፓርኩ ተቋሙን ከኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር የፈጠራና የምርምር ግኝቶች ወደ ውጤት እንዲቀየሩ የሚያደርግ ነው።
ይህም ሀገርን በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በፈጠራ ወደፊት ለማምጣት የሚደረገውን ጥረት ያግዛል ብለዋል።
በዩኒቨርሲቲው ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት ፕሮጀክቶች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ምሳሌ መሆናቸውንም አቶ ኮራ ጠቅሰዋል።

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ለሚ ጉታ(ዶ/ር) በበኩላቸው ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት አምስት ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ፕሮጀክቶቹ ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ብቁ የሰው ሃይል ለማፍራት እንዲሁም በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በሳይንስ ዘርፍ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት የሚያስችሉ ናቸው ሲሉም ተናግረዋል።
በተለይ የማህበረሰብ ትምህርት ቤቶቹ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ልጆቹ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችሉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለጻ ዛሬ ለምረቃ የበቁት ፕሮጀክቶች ባለ አራት ወለል የቢዝነስ ማዕከል ህንፃ፣ መኖሪያ ቤቶች፣ የህፃናት ማቆያ ማዕከል፣ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ የማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም የመምህራንና የሠራተኞች የመዝናኛ ማዕከል ናቸው።
ከእነዚህ በተጨማሪ 14 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ፣ የአይሲቲ እና የዳታ ማዕከል፣ ሁለገብ የስብሰባ ማዕከልና ሕንጻዎች እንዲሁም የምርምርና የቴክኖሎጂ ፓርኩ በቅርቡ ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቁ ተመላክቷል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026