
ባህርዳር፤የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ዘርፍ አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለጹ።
የአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ክልላዊ የግብርና ምርምር ስራዎች አውደ ጥናት በባህርዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪና ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር)፤ በሁሉም የግብርና ምርቶች ምርትና ምርታማነት ከፍተኛ መሻሻል ማሳየቱን ገልጸዋል።
በክልሉ ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው መድረኩ ለዚህ ትልቅ ግብአት እንደሚሆንም ገልጸዋል።
የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ አረጋግጠዋል።
የአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስማረ ደጀን (ዶ/ር)፣ ኢንስቲትዩቱ የክልሉንና የሀገሪቱን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ቀናት በሚካሄደው የምርምር ስራዎች አውደ ጥናትም በርካታ የምርምር ስራዎች ቀርበው የሚገመገሙ መሆኑን ጠቁመዋል።
በምርምር የሚፈልቁ የሰብል፣ የእንስሳት፣ የመስኖ፣ የተፈጥሮ ሃብትና ሌሎችም ግኝቶች ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ ተጠቃሚ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።
በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርና እና የአካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ፕሮፌሰር መልካሙ አለማየሁ፤ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የምርመር ዘርፎች ከኢንስቲትዩቱ ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዓመታዊው የምርምር አውደጥናት ላይ በርካታ የዘርፉ ተመራማሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026