
ባህርዳር፤የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የገጠር ዘርፍ አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለጹ።
የአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ክልላዊ የግብርና ምርምር ስራዎች አውደ ጥናት በባህርዳር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪና ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር)፤ በሁሉም የግብርና ምርቶች ምርትና ምርታማነት ከፍተኛ መሻሻል ማሳየቱን ገልጸዋል።
በክልሉ ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው መድረኩ ለዚህ ትልቅ ግብአት እንደሚሆንም ገልጸዋል።
የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችም ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ አረጋግጠዋል።
የአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አስማረ ደጀን (ዶ/ር)፣ ኢንስቲትዩቱ የክልሉንና የሀገሪቱን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ቀናት በሚካሄደው የምርምር ስራዎች አውደ ጥናትም በርካታ የምርምር ስራዎች ቀርበው የሚገመገሙ መሆኑን ጠቁመዋል።
በምርምር የሚፈልቁ የሰብል፣ የእንስሳት፣ የመስኖ፣ የተፈጥሮ ሃብትና ሌሎችም ግኝቶች ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ ተጠቃሚ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።
በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርና እና የአካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ፕሮፌሰር መልካሙ አለማየሁ፤ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የምርመር ዘርፎች ከኢንስቲትዩቱ ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዓመታዊው የምርምር አውደጥናት ላይ በርካታ የዘርፉ ተመራማሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026