የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ፖሊሲው የምግብ ዋስትናና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 24/2017 (ኢዜአ) :- አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ የምግብ ዋስትናና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና እንደሚጫወት ተገለጸ።

አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲን ማስተዋወቂያ መድረክ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል ፡፡


የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ በየነ በራሳ በወቅቱ እንደገለጹት አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ከዚህ በፊት ጥቅም ላይ ሲውል በቆየው ፖሊሲ ውስጥ የነበሩ ክፍተቶችን የሚሞላና ያለውን የዕድገት ደረጃ የሚመጥን ነው ፡፡

ፖሊሲው የገጠሩን ክፍለ ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር በማምጣት የምግብ ዋስትናና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡

በሲዳማ ክልል ካለው የመሬት ጥበትና ተፈጥሯዊ ሥነ-ምህዳር ጋር የሚዛመዱ የእርሻ ፣ የእንስሳት ሀብትና ሌሎች ፓኬጆች ተቀርፀው በትግበራ ላይ መሆናቸውን አውስተዋል ፡፡

ፖሊሲው ተግባራቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል ጠቀሜታው የላቀ መሆኑን አስታውቀዋል ።

የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው "ፖሊሲው ከዚህ በፊት ትኩረት ተነፍጎት ለነበረው የግሉ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የወጠናቸውን የልማት ግቦች ለማሳካት ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው "ብለዋል ፡፡

ለአብነት በአሁን ወቅት በክልሉ አምስት የግል ድርጅቶች በምርጥ ዘር ብዜት ሥራ ላይ ተሰማርተው 10 በመቶ የሚሆነውን የክልሉ ፍላጎት መሸፈን መቻላቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ዘርፉን በተገቢው መንገድ በማበረታታት የአርሶ አደሩን የግብዐት ችግሮች በዘለቄታው መቅረፍ እንደሚቻል ጠቅሰዋል ፡፡

በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የፖሊሲ ጥናትና የሥርዐተ ምግብ ዳይሬክተር አቶ ረታ ዋጋሪ "ላለፉት 22 ዓመታት በሥራ ላይ የቆየው ፖሊሲ የኤክስቴንሽን ሥርዐትን ከማዘመን ፣ በርካታ ባለሙያዎችን ከማፍራት እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አኳያ ውጤቶች ተገኝተውበታል" ብለዋል ፡፡

ሆኖም ያሉበትን ክፍተቶች ለመሙላት፣ በውስጡ ያልተካተቱ ሀሳቦችን ለመጨመር እንዲሁም የዘርፉን እድገት ደረጃና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን የተመለከቱ ጉዳዮችን ለማካተት አዲሱን ፖሊሲ መቅረፅ እንዳስፈለገ ጠቅሰዋል ፡፡

ፖሊሲው በጥቅሉ በምርትና ምርታማነት፣ በአርሶ አደሩ ሕይወት፣ በሥርዐተ ምግብ፣ በምግብ ዋስትና ፣ ግብርናን ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በማስተጋበር ረገድ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን ያስቀመጠ መሆኑን አመልክተዋል።

በመድረኩ ላይ ኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልል የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026