
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡-የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አመራሮች በጃፓን ቶኪዮ እየተካሄደ ባለው በ33ኛው የእስያ፤ አረብና አፍሪካ የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ የኢትዮጵያ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን ጸጋ ለባለሀብቶች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

ባለሀብቶቹ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎታቸውን አሳይተዋል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) መንግስት የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለዉጭ ባለሀብቶች የበለጠ ቀልጣፋ፤ ሳቢ እና ተመራጭ ለማድረግ የወሰዳቸዉን የፖሊሲ ማበረታቻዎች፤ ሀገር በቀል የሪፎርም ስራዎችን በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖቹ ዉስጥ ያሉ የአንድ መስኮት አገልግሎቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ኢትዮጵያ ሰፊ ወጣት የሰው ኃይል ያላት ሀገር መሆኗ ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እንድትሆን አድርጓታል ሲሉ ገልጸዋል።
ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸዉ የልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችና የነጻ ንግድ ቀጣና ዉስጥ ዘመናዊ መሰረተ ልማቶች መሟላታቸውን አመልክተዋል።
በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል በተመጣጣኝ ዋጋ ለኢንቨስተሮች መቅረቡ፣ ምቹ መልክዐ ምድራዊ አቀማመጥ፣ሰፊ የገበያ እድል መኖሩ ኢትዮጵያን ለዓለም አቀፍ ባለሃብቶች የበለጠ ተመራጭ መዳረሻ ያደርጋታል ብለዋል።

በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌ በበኩላቸዉ ኢትዮጵያ በበርካታ መመዘኛዎች ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ሀገር ሆናለች ሲሉ ተናግረዋል።
መንግስት ከዚህ ቀደም የኢንቨስትመንት ዘርፉ ዋነኛ ማነቆ የነበሩ ችግሮችን በመለየት የወሰዳቸዉ እርምጃዎችና የፖሊሲ ማሻሻያዎች በአጭር ጊዜ ለውጥ እያመጡ እንደሆነ መግለጻቸውን ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026