የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>ኮርፖሬሽኑ የኢትዮጵያ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን ጸጋ በጃፓን በማስተዋወቅ ላይ ነው</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡-የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አመራሮች በጃፓን ቶኪዮ እየተካሄደ ባለው በ33ኛው የእስያ፤ አረብና አፍሪካ የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ የኢትዮጵያ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችን ጸጋ ለባለሀብቶች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛሉ፡፡


ባለሀብቶቹ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎታቸውን አሳይተዋል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) መንግስት የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለዉጭ ባለሀብቶች የበለጠ ቀልጣፋ፤ ሳቢ እና ተመራጭ ለማድረግ የወሰዳቸዉን የፖሊሲ ማበረታቻዎች፤ ሀገር በቀል የሪፎርም ስራዎችን በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖቹ ዉስጥ ያሉ የአንድ መስኮት አገልግሎቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ኢትዮጵያ ሰፊ ወጣት የሰው ኃይል ያላት ሀገር መሆኗ ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እንድትሆን አድርጓታል ሲሉ ገልጸዋል።

ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸዉ የልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችና የነጻ ንግድ ቀጣና ዉስጥ ዘመናዊ መሰረተ ልማቶች መሟላታቸውን አመልክተዋል።

በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል በተመጣጣኝ ዋጋ ለኢንቨስተሮች መቅረቡ፣ ምቹ መልክዐ ምድራዊ አቀማመጥ፣ሰፊ የገበያ እድል መኖሩ ኢትዮጵያን ለዓለም አቀፍ ባለሃብቶች የበለጠ ተመራጭ መዳረሻ ያደርጋታል ብለዋል።


በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌ በበኩላቸዉ ኢትዮጵያ በበርካታ መመዘኛዎች ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ሀገር ሆናለች ሲሉ ተናግረዋል።

መንግስት ከዚህ ቀደም የኢንቨስትመንት ዘርፉ ዋነኛ ማነቆ የነበሩ ችግሮችን በመለየት የወሰዳቸዉ እርምጃዎችና የፖሊሲ ማሻሻያዎች በአጭር ጊዜ ለውጥ እያመጡ እንደሆነ መግለጻቸውን ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026