
ነገሌ ቦረና፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ቦረና ዞን ከ158 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለበልግ አዝመራ መዘጋጀቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በምሥራቅ ቦረና ዞን ከሚያዝያ ወር ጀምሮ የዝናብና የበልግ አዝመራ ወቅት መሆኑ ይታወቃል፡፡
በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ በዘንድሮው ዓመት ከ158 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለበልግ አዝመራ የተዘጋጀ ሲሆን፤ እስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴ 70 ሺህ 300 ሄክታር መሬት ለሶስተኛ ዙር ታርሶ ለዘር ተዘጋጅቷል፡፡

በዘንድሮው ዓመት ለበልግ አዝመራ የተዘጋጀው አጠቃላይ መሬት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ16 ሺህ 135 ሄክታር እንደሚበልጥም ተናግረዋል፡፡
ከዞኑ የበልግ አዝመራ ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ አጠቃላይ ምርት ለመሰብሰብ የታቀደ ሲሆን በዞኑ ስምንት ወረዳዎች 41 ሺህ 427 አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች የማሳ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሆኑም ተናግረዋል፡፡

በጽህፈት ቤቱ የግብአት ስርጭትና አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ አብዱረሂም አብዱረህማን በበኩላቸው እስካሁን 13 ሺህ 580 ኩንታል ማዳበሪያ ተሰራጭቷል ብለዋል፡፡
በዞኑ ስምንት ወረዳዎች ለዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከ104 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተጨማሪም ከ28 ሺህ ኩንታል በላይ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ የተባዛ የአከባቢው ዘር ማዘጋጀታቸውን አረጋግጠናል ብለዋል፡፡

የነገሌ ቦረና ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አቶ ብርቁ በላቸው የመኸሩ ዝናብ ቆይታ አጭር ስለነበር የጠበቁትን ያክል ምርት እንዳላገኙ ያስታውሳሉ፡፡
በመኸር አዝመራው የጎደለውን ምርት በተያዘው የበልግ እርሻ ለማካካስ ከአራት ሄክታር በላይ መሬት ደጋግመው በማረስ በጤፍ ዘር ለመሸፈን ተዘጋጅተዋል፡፡
ምርትና ምርታመነትን ለማሳደግም ስምንት ኩንታል የአከባቢ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ አዘጋጅቻለሁ ብለዋል፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026