የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በምሥራቅ ቦረና ዞን ከ158 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለበልግ አዝመራ ተዘጋጅቷል</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ቦረና ዞን ከ158 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለበልግ አዝመራ መዘጋጀቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡

በምሥራቅ ቦረና ዞን ከሚያዝያ ወር ጀምሮ የዝናብና የበልግ አዝመራ ወቅት መሆኑ ይታወቃል፡፡

በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ በዘንድሮው ዓመት ከ158 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለበልግ አዝመራ የተዘጋጀ ሲሆን፤ እስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴ 70 ሺህ 300 ሄክታር መሬት ለሶስተኛ ዙር ታርሶ ለዘር ተዘጋጅቷል፡፡


በዘንድሮው ዓመት ለበልግ አዝመራ የተዘጋጀው አጠቃላይ መሬት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ16 ሺህ 135 ሄክታር እንደሚበልጥም ተናግረዋል፡፡

ከዞኑ የበልግ አዝመራ ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ አጠቃላይ ምርት ለመሰብሰብ የታቀደ ሲሆን በዞኑ ስምንት ወረዳዎች 41 ሺህ 427 አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች የማሳ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሆኑም ተናግረዋል፡፡


በጽህፈት ቤቱ የግብአት ስርጭትና አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ አብዱረሂም አብዱረህማን በበኩላቸው እስካሁን 13 ሺህ 580 ኩንታል ማዳበሪያ ተሰራጭቷል ብለዋል፡፡

በዞኑ ስምንት ወረዳዎች ለዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከ104 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተጨማሪም ከ28 ሺህ ኩንታል በላይ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ የተባዛ የአከባቢው ዘር ማዘጋጀታቸውን አረጋግጠናል ብለዋል፡፡


የነገሌ ቦረና ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አቶ ብርቁ በላቸው የመኸሩ ዝናብ ቆይታ አጭር ስለነበር የጠበቁትን ያክል ምርት እንዳላገኙ ያስታውሳሉ፡፡

በመኸር አዝመራው የጎደለውን ምርት በተያዘው የበልግ እርሻ ለማካካስ ከአራት ሄክታር በላይ መሬት ደጋግመው በማረስ በጤፍ ዘር ለመሸፈን ተዘጋጅተዋል፡፡

ምርትና ምርታመነትን ለማሳደግም ስምንት ኩንታል የአከባቢ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ አዘጋጅቻለሁ ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026