የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>በምሥራቅ ቦረና ዞን ከ158 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለበልግ አዝመራ ተዘጋጅቷል</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ቦረና ዞን ከ158 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለበልግ አዝመራ መዘጋጀቱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡

በምሥራቅ ቦረና ዞን ከሚያዝያ ወር ጀምሮ የዝናብና የበልግ አዝመራ ወቅት መሆኑ ይታወቃል፡፡

በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ቦነያ ሁቃ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ በዘንድሮው ዓመት ከ158 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለበልግ አዝመራ የተዘጋጀ ሲሆን፤ እስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴ 70 ሺህ 300 ሄክታር መሬት ለሶስተኛ ዙር ታርሶ ለዘር ተዘጋጅቷል፡፡


በዘንድሮው ዓመት ለበልግ አዝመራ የተዘጋጀው አጠቃላይ መሬት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ16 ሺህ 135 ሄክታር እንደሚበልጥም ተናግረዋል፡፡

ከዞኑ የበልግ አዝመራ ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ አጠቃላይ ምርት ለመሰብሰብ የታቀደ ሲሆን በዞኑ ስምንት ወረዳዎች 41 ሺህ 427 አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች የማሳ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሆኑም ተናግረዋል፡፡


በጽህፈት ቤቱ የግብአት ስርጭትና አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ አብዱረሂም አብዱረህማን በበኩላቸው እስካሁን 13 ሺህ 580 ኩንታል ማዳበሪያ ተሰራጭቷል ብለዋል፡፡

በዞኑ ስምንት ወረዳዎች ለዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከ104 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተጨማሪም ከ28 ሺህ ኩንታል በላይ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ የተባዛ የአከባቢው ዘር ማዘጋጀታቸውን አረጋግጠናል ብለዋል፡፡


የነገሌ ቦረና ዙሪያ ወረዳ ነዋሪ አቶ ብርቁ በላቸው የመኸሩ ዝናብ ቆይታ አጭር ስለነበር የጠበቁትን ያክል ምርት እንዳላገኙ ያስታውሳሉ፡፡

በመኸር አዝመራው የጎደለውን ምርት በተያዘው የበልግ እርሻ ለማካካስ ከአራት ሄክታር በላይ መሬት ደጋግመው በማረስ በጤፍ ዘር ለመሸፈን ተዘጋጅተዋል፡፡

ምርትና ምርታመነትን ለማሳደግም ስምንት ኩንታል የአከባቢ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ አዘጋጅቻለሁ ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026