አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-የጃፓን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች መሰማራት እንደሚፈልጉ አስታወቁ።
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ(ዶ/ር) ከተለያዩ የጃፓን ኩባንያዎች ጋር በቶኪዮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውይይት አድርገዋል።
በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ዕድሎችና አስቻይ ሁኔታዎችን አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት ዋና ስራ አስፈጻሚው፥ ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌ፥ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያና ጃፓን ግንኙነት በኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፍ ይበልጥ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ የተለያዩ የኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጠይቀዋል።
ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ በተለይም በኢነርጂና ኮስሞቲከስ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን በቶኪዮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025