
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-የጃፓን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች መሰማራት እንደሚፈልጉ አስታወቁ።
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ(ዶ/ር) ከተለያዩ የጃፓን ኩባንያዎች ጋር በቶኪዮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውይይት አድርገዋል።
በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ዕድሎችና አስቻይ ሁኔታዎችን አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት ዋና ስራ አስፈጻሚው፥ ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።

በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌ፥ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያና ጃፓን ግንኙነት በኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፍ ይበልጥ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ የተለያዩ የኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጠይቀዋል።
ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ በተለይም በኢነርጂና ኮስሞቲከስ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን በቶኪዮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026