
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-የጃፓን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች መሰማራት እንደሚፈልጉ አስታወቁ።
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ(ዶ/ር) ከተለያዩ የጃፓን ኩባንያዎች ጋር በቶኪዮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውይይት አድርገዋል።
በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ዕድሎችና አስቻይ ሁኔታዎችን አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት ዋና ስራ አስፈጻሚው፥ ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።

በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌ፥ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያና ጃፓን ግንኙነት በኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፍ ይበልጥ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ የተለያዩ የኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጠይቀዋል።
ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ በተለይም በኢነርጂና ኮስሞቲከስ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን በቶኪዮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026