
አዲስ አበባ፤ የካቲት 26/2017(ኢዜአ)፡-የጃፓን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች መሰማራት እንደሚፈልጉ አስታወቁ።
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ(ዶ/ር) ከተለያዩ የጃፓን ኩባንያዎች ጋር በቶኪዮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውይይት አድርገዋል።
በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ዕድሎችና አስቻይ ሁኔታዎችን አስመልክቶ ገለፃ ያደረጉት ዋና ስራ አስፈጻሚው፥ ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።

በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌ፥ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያና ጃፓን ግንኙነት በኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፍ ይበልጥ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ የተለያዩ የኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጠይቀዋል።
ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ በተለይም በኢነርጂና ኮስሞቲከስ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን በቶኪዮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026