የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የገጠር ትስስር ተደራሽነትን ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም ውጤታማነት ለመጠቀም የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፦የገጠር ትስስር ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም ውጤታማነት ለማዋል የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡


ሚኒስቴሩ ከኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የገጠር ትስስርን ከምግብ ዋስትና ፕሮግራም ትግበራ ጋር ለማሳለጥ በተዘጋጀው መመሪያ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለባለድርሻ አካላት መስጠት ጀምሯል፡፡


የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት በዚሁ ወቅት፤ የገጠር መንገድ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


የሀገሪቱን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ማሳለጥ ለሚያስችሉ የመንገድ መሠረተ ልማቶችን ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


የገጠር መንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት በዓለም ባንክ ድጋፍ በክልሎች ተግባራዊ የሚደረግ ፕሮጀክት ይፋ መደረጉንም አውስተዋል።


በፕሮጀክቱም የአዳዲስ የመንገድ ግንባታዎች እና የገጠር መንገድ ጥገና ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


ፕሮጀክቶቹን በአምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ መያዙን ጠቁመው በተቻለ አቅም ከተያዘላቸው ጊዜ ቀድሞ በማጠናቀቅ ወደ አገልግሎት እንዲገቡ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።


ይህም ለማህበረሰቡ ምቹ የመንገድ ተደራሽነትን ለመፍጠር ብሎም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በስልጠናው ላይ የተገኙት የክልል ባለድርሻ አካላት ፕሮጀክቶቹን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ታደሰ ይርዳው የክልሉን ህዝብ የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በመንግስት በጀት ከሚሰሩ ልማቶች በተጨማሪ ከአጋር ድርጅቶች በሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


የትግራይ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሲሳይ አማረ በበኩላቸው በፕሮገራሙ ስምንት ወረዳዎች ተደራሽ እንደሚሆኑ ጠቅሰው፤ ከወረዳዎቹ መካከልም በዚህ አመት በሁለቱ ላይ እንደሚሰራ አመላክተዋል፡፡


የኦሮሚያ መንገዶችና ሎጅስቲክስ ቢሮ ሃላፊ ኢንጅነር ሄለን ታምሩ እንዳሉት በፕሮግራሙ የሚገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች በተያዘላቸው ጊዜ እና በጥራት ተሰርተው ለአገልግሎት እንዲበቁ ክትትል እንደሚደረግ ነው የተናገሩት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025