የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

<p>የገጠር ትስስር ተደራሽነትን ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም ውጤታማነት ለመጠቀም የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፦የገጠር ትስስር ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም ውጤታማነት ለማዋል የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡


ሚኒስቴሩ ከኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የገጠር ትስስርን ከምግብ ዋስትና ፕሮግራም ትግበራ ጋር ለማሳለጥ በተዘጋጀው መመሪያ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለባለድርሻ አካላት መስጠት ጀምሯል፡፡


የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት በዚሁ ወቅት፤ የገጠር መንገድ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


የሀገሪቱን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ማሳለጥ ለሚያስችሉ የመንገድ መሠረተ ልማቶችን ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


የገጠር መንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት በዓለም ባንክ ድጋፍ በክልሎች ተግባራዊ የሚደረግ ፕሮጀክት ይፋ መደረጉንም አውስተዋል።


በፕሮጀክቱም የአዳዲስ የመንገድ ግንባታዎች እና የገጠር መንገድ ጥገና ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


ፕሮጀክቶቹን በአምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ መያዙን ጠቁመው በተቻለ አቅም ከተያዘላቸው ጊዜ ቀድሞ በማጠናቀቅ ወደ አገልግሎት እንዲገቡ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።


ይህም ለማህበረሰቡ ምቹ የመንገድ ተደራሽነትን ለመፍጠር ብሎም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በስልጠናው ላይ የተገኙት የክልል ባለድርሻ አካላት ፕሮጀክቶቹን በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ታደሰ ይርዳው የክልሉን ህዝብ የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በመንግስት በጀት ከሚሰሩ ልማቶች በተጨማሪ ከአጋር ድርጅቶች በሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


የትግራይ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሲሳይ አማረ በበኩላቸው በፕሮገራሙ ስምንት ወረዳዎች ተደራሽ እንደሚሆኑ ጠቅሰው፤ ከወረዳዎቹ መካከልም በዚህ አመት በሁለቱ ላይ እንደሚሰራ አመላክተዋል፡፡


የኦሮሚያ መንገዶችና ሎጅስቲክስ ቢሮ ሃላፊ ኢንጅነር ሄለን ታምሩ እንዳሉት በፕሮግራሙ የሚገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች በተያዘላቸው ጊዜ እና በጥራት ተሰርተው ለአገልግሎት እንዲበቁ ክትትል እንደሚደረግ ነው የተናገሩት፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው &quot;ቡኖ - ማላ&quot; ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026