
መቀሌ፤ የካቲት26/2017 (ኢዜአ) ፡-በትግራይ ክልል በልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር የታቀፉ ወገኖች በዘላቂነት እንዲቋቋሙ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለጸ።
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አልማዝ ገብረፃዲቅ ለኢዜአ እንደገለፁት በክልሉ በአምስት ከተሞች የምግብ ዋስትና ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ተግባራዊ እየተደረገ ነው።
በዚህም ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን በልማታዊ ሴፍቲኔት በማቀፍ ሰርተው እንዲለወጡ የማድረግ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል።
በመጀመሪያው ዙር የከተሞች የምግብ ዋስትና ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በአምስት ከተሞች ከ34 ሺህ 600 በላይ ዜጎች መታቀፋቸውን አስታውሰው በግማሽ በጀት ዓመቱ ሰርተው ለሚከፈላቸውና በቀጥታ ለሚደገፉ ወገኖች ከፌደራል መንግስት የተላከ 14 ሚሊዮን ብር ስራ ላይ መዋሉን ገልፀዋል።

በሁለተኛው ዙር የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚዎችም ሰርተው በመለወጥ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እንዲችሉ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ከመርሃ ግብሩ ተጠቃሚዎች መካከል በመቀሌ ከተማ የሚኖሩት ወይዘሮ መሰረት ገብረ እግዚአብሔር፤ በወር ሰርተው ከሚከፈላቸው ወርሃዊ ደሞዝ 20 በመቶውን በመቆጠብ ህይወታቸውን በዘላቂነት ለማሻሻል ጥረት እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል።
ሌላኛዋ የከተማው ነዋሪ ወጣት ዛይድ አለምሰገድ፤ በአረንጓዴ ልማት ላይ በመሰማራት በተለይ የተተከሉ ችግኞች እና የውበት ስፍራዎች በመንከባከብ በወር አምስት ሺህ ብር እንደምታገኝ ተናግራለች።

በመርሃ ግብሩ ሰርተን መለወጥ እንደምንችል ጥሩ አጋጣሚ በመሆኑ ለስኬት እየተጋን እንገኛለን ብላለች።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026