አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ሁሉን አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት የሚያስችሉ ስራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዝያ አሚን(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም እና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር ለሴቶች እና ወጣቶች የዲጂታል ፋይናንሻል አገልግሎት ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀ እና የዲጂታል አቅምን ማጎልበት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዝያ አሚን (ዶ/ር) መንግስት በኢትዮጵያ አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ለዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
የሴቶችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ የዲጂታል ኢኮኖሚ እድገትን ማፋጠን እንደሚገባም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝ ጠቅሰው ሴቶች በዲጂታል ኢኮኖሚ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተዋል።
ስልጠናው በዲጂታል ባንክ አገልግሎትና በዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት እድሎችና ተግዳሮቶች፣ ሞባይል ባንኪንግ፣ የቴሌ ብር አገልግሎት ለሴቶች እና ሌሎች ተጓዳኝ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025