
አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ሁሉን አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት የሚያስችሉ ስራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዝያ አሚን(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም እና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር ለሴቶች እና ወጣቶች የዲጂታል ፋይናንሻል አገልግሎት ስልጠና ሰጥቷል።

ስልጠናው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት የተዘጋጀ እና የዲጂታል አቅምን ማጎልበት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ፎዝያ አሚን (ዶ/ር) መንግስት በኢትዮጵያ አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ለዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
የሴቶችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ የዲጂታል ኢኮኖሚ እድገትን ማፋጠን እንደሚገባም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝ ጠቅሰው ሴቶች በዲጂታል ኢኮኖሚ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተዋል።
ስልጠናው በዲጂታል ባንክ አገልግሎትና በዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት እድሎችና ተግዳሮቶች፣ ሞባይል ባንኪንግ፣ የቴሌ ብር አገልግሎት ለሴቶች እና ሌሎች ተጓዳኝ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026