አዲስ አበባ፤ የካቲት 29 /2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ግምታቸው ከ939 ሚሊዮን ብር የሆኑ የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን አስታወቀ፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ የተያዙት ከየካቲት 21 እስከ 27 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ክትትል መሆኑንም ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡
በዚህም 573 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር የገቢ እና 365 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎች፤ በድምሩ 939 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች መያዛቸውን ነው ያስታወቀው፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል የተለያዩ ማዕድናት፣ አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ ጥራጥሬ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድኃኒት፣ የቁም እንስሳት እና የውጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል።
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ እና በበረራ የተያዙ መሆናቸውን ገልጿል።
የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ ዘጠኝ ተጠርጣሪ ግለሰቦች እና ሶስት ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል።
የኮንትሮባንድ እና ሕገ-ወጥ ንግድ ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ ለመከላከል ሁሉም ባለድርሻ አካላትና ሕብረተሰቡ የበኩላቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025