
ሆሳዕና፤ የካቲት 30/2017 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተሞችን ፅዱ፣ ውብና ተወዳዳሪ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
በሆሳዕና ከተማ ለኮሪደር ልማትና ሌሎች ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የገቢ ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ከተሞችን ፅዱ፣ ውብ፣ ተወዳዳሪና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
በክልሉ ባሉ ሰባት የክላስተር ማዕከል ከተሞች ከ165 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ ልማቱ ከተሞችን ውብና ተወዳዳሪ ከማድረግ ባለፈ ለነዋሪዎች ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ ለዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የህብረተሰቡን የሥራ ባህል እየቀየረ መሆኑን የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከተሞችን ምቹና ተወዳዳሪ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
የሆሳዕና ከተማን ጨምሮ በሌሎች የክልሉ ከተሞች እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራን ጨምሮ ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ፣ የህብረተሰቡ ተሳትፎ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል።
የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዳዊት ጡምደዶ በበኩላቸው፣ በከተማ አስተዳደሩና በህዝብ ተሳትፎ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቶቹ የከተማዋን ገጽታ የሚቀይሩና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታቸው ከፍተኛ መሆኑንም አስረድተዋል።
የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የወጣቶች መዝናኛና ሌሎች ፕሮጀክቶች ከተማዋን ተወዳዳሪና ለኑሮ ተመራጭ የሚያደርጉ መሆናቸውን ጠቁመው፣ አስተዳደሩ ልማቱ እንዲፋጠን የጀመረውን ጥረት ያጠናክራል ብለዋል፡፡

የልማት ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው የጊዜ ገደብና ጥራት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማዋል ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፣ በልማቱ የህዝብ ተሳትፎን ለማጠናከር የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብሩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች የክልሉና የሀድያ ዞን አመራሮች እንዲሁም ባለሀብቶችና የንግዱ ማህበረሰብ አካላት እየተሳተፉ ነው፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026