የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የወተት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው - ግብርና ሚኒስቴር

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት የወተት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በዝርያ ማዳቀል፣ በመኖ ልማት፣ በወተት ማቀነባበርና በገበያ ትስስር ላይ መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ግብርና ሚኒስቴር ገልጿል።

ባለፉት ዓመታት የወተት ምርታማነትን ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤት መመዝገቡን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የወተት ልማት ምርታማነት እና ኢኖቬሽን ላይ ያተኮረ ውይይት ዛሬ ተካሂዷል።

በዚሁ ወቅት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) እንዳሉት የወተት ምርትን የበለጠ ማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።


የወተት ምርታማነትን የበለጠ ለማሳደግ የባለድርሻ አካላት ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በቀጣይ ዘርፉን በምርምር መደገፍ፣ ስራዎችን በጋራ መስራት እና የሌሎች ሀገራት ተሞክሮዎችን በመቅሰም ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

የሌማት ትሩፋት መርኃ ግብር ከመጀመሩ በፊት ዓመታዊ የወተት ምርት 5 ነጥብ 8 ቢሊየን ሊትር እንደነበር ገልፀው በዚህ ዓመት መጨረሻ ዓመታዊ የወተት ምርትን 12 ቢሊየን ሊትር ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ ዓመት 3 ነጥብ 8 ሚሊየን ላሞችን ለማዳቀል መታቀዱን አስታውቀው እስከ አሁን 2 ሚሊየን ላሞችን ማዳቀል መቻሉን ተናግረዋል።

መንግስት የወተት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በዝርያ ማዳቀል፣ በመኖ ልማት፣ በወተት ማቀነባበር እና በገበያ ትስስር ላይ መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

የወተት ምርታማነትን በምርምር ለማሳደግ የወተት ላም ዝርያዎች ማሻሻል የሚያስችሉ ስራዎች በመስራት የተሻለ ውጤት መገኘቱን ጠቁመዋል።

ተጨማሪ አምስት አዳዲስ የፈሳሽ ናይትሮጂን ማምረቻ የዝርያ ማሻሻያ ማዕከላት በተለያዩ ከተሞች ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በዚህም ላሞችን ከማዳቀል እስከ ወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ግንባታ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።


የዓለም አቀፉ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር ገብረእግዚአብሔር ገብረዮሃንስ ከሚኒስቴሩ ጋር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ ዝርያ ለማሻሻል፣ የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተጀመሩ ስራዎች የበለጠ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026