የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአዳማ ከተማ በግማሽ ዓመት ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ተፈጥሯል

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ )፡- በአዳማ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን የከተማ አስተዳደሩ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የከተማዋ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልቃድር ጠይብ፤ በከተማዋ በስራ እድል ፈጠራ የተከናወኑ ስራዎችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት በተለያዩ መስኮች ለ31 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም በግብርና፣ በወተት ልማት፣ በዶሮና በንብ ማነብ፣ በዓሳ እንዲሁም በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለብዙዎች የስራ እድል መፈጠሩን አንስተዋል።

በግማሽ ዓመቱ ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግረው በከተማዋ የዓሣ እርባታ ኩሬዎችና የንብ ማነቢያ ቀፎዎች ለወጣቶች መተላለፋቸውን ጠቅሰዋል።

እንዲሁም የወተት ላሞችና የዶሮ እርባታ ማዕከላት መገንባታቸውን ያነሱት ሀላፊው እንዲሁም የማምረቻ ማእከላት መሰራታቸውንም ገልፀዋል።

እኒሼቲቮቹን ውጤታማ ለማድረግ ከተማ አስተዳድሩ የውሃ፣ መብራትና የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ማሟላቱን ተናግረዋል።

ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር የፋይናንስ አቅርቦቱን ሟሟላት መቻሉንም ተናግረው በዚህም መሰረት 264 ሚሊዮን ብር ለ166 ማህበራት ብድር መሰጠት ተችሏል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025