
አዳማ ፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ )፡- በአዳማ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን የከተማ አስተዳደሩ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የከተማዋ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልቃድር ጠይብ፤ በከተማዋ በስራ እድል ፈጠራ የተከናወኑ ስራዎችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት በተለያዩ መስኮች ለ31 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።
በዚህም በግብርና፣ በወተት ልማት፣ በዶሮና በንብ ማነብ፣ በዓሳ እንዲሁም በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለብዙዎች የስራ እድል መፈጠሩን አንስተዋል።
በግማሽ ዓመቱ ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግረው በከተማዋ የዓሣ እርባታ ኩሬዎችና የንብ ማነቢያ ቀፎዎች ለወጣቶች መተላለፋቸውን ጠቅሰዋል።
እንዲሁም የወተት ላሞችና የዶሮ እርባታ ማዕከላት መገንባታቸውን ያነሱት ሀላፊው እንዲሁም የማምረቻ ማእከላት መሰራታቸውንም ገልፀዋል።
እኒሼቲቮቹን ውጤታማ ለማድረግ ከተማ አስተዳድሩ የውሃ፣ መብራትና የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ማሟላቱን ተናግረዋል።
ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር የፋይናንስ አቅርቦቱን ሟሟላት መቻሉንም ተናግረው በዚህም መሰረት 264 ሚሊዮን ብር ለ166 ማህበራት ብድር መሰጠት ተችሏል ብለዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026