የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአዳማ ከተማ በግማሽ ዓመት ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ተፈጥሯል

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ )፡- በአዳማ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን የከተማ አስተዳደሩ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የከተማዋ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልቃድር ጠይብ፤ በከተማዋ በስራ እድል ፈጠራ የተከናወኑ ስራዎችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት በተለያዩ መስኮች ለ31 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም በግብርና፣ በወተት ልማት፣ በዶሮና በንብ ማነብ፣ በዓሳ እንዲሁም በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለብዙዎች የስራ እድል መፈጠሩን አንስተዋል።

በግማሽ ዓመቱ ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግረው በከተማዋ የዓሣ እርባታ ኩሬዎችና የንብ ማነቢያ ቀፎዎች ለወጣቶች መተላለፋቸውን ጠቅሰዋል።

እንዲሁም የወተት ላሞችና የዶሮ እርባታ ማዕከላት መገንባታቸውን ያነሱት ሀላፊው እንዲሁም የማምረቻ ማእከላት መሰራታቸውንም ገልፀዋል።

እኒሼቲቮቹን ውጤታማ ለማድረግ ከተማ አስተዳድሩ የውሃ፣ መብራትና የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ማሟላቱን ተናግረዋል።

ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር የፋይናንስ አቅርቦቱን ሟሟላት መቻሉንም ተናግረው በዚህም መሰረት 264 ሚሊዮን ብር ለ166 ማህበራት ብድር መሰጠት ተችሏል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026