የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአዳማ ከተማ በግማሽ ዓመት ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ተፈጥሯል

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ )፡- በአዳማ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን የከተማ አስተዳደሩ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የከተማዋ የስራ እድል ፈጠራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አብዱልቃድር ጠይብ፤ በከተማዋ በስራ እድል ፈጠራ የተከናወኑ ስራዎችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት በተለያዩ መስኮች ለ31 ሺህ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም በግብርና፣ በወተት ልማት፣ በዶሮና በንብ ማነብ፣ በዓሳ እንዲሁም በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለብዙዎች የስራ እድል መፈጠሩን አንስተዋል።

በግማሽ ዓመቱ ከ41 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግረው በከተማዋ የዓሣ እርባታ ኩሬዎችና የንብ ማነቢያ ቀፎዎች ለወጣቶች መተላለፋቸውን ጠቅሰዋል።

እንዲሁም የወተት ላሞችና የዶሮ እርባታ ማዕከላት መገንባታቸውን ያነሱት ሀላፊው እንዲሁም የማምረቻ ማእከላት መሰራታቸውንም ገልፀዋል።

እኒሼቲቮቹን ውጤታማ ለማድረግ ከተማ አስተዳድሩ የውሃ፣ መብራትና የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ማሟላቱን ተናግረዋል።

ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር የፋይናንስ አቅርቦቱን ሟሟላት መቻሉንም ተናግረው በዚህም መሰረት 264 ሚሊዮን ብር ለ166 ማህበራት ብድር መሰጠት ተችሏል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026