የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በማስፋፊያ ሥራ ተጨማሪ 310 ሜጋ ዋት ኃይል ማግኘት ተችሏል - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት አምስት ዓመታት በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በተከናወኑ የማስፋፊያ ስራዎች ተጨማሪ 310 ሜጋ ዋት ኃይል ማግኘት መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል አስታወቀ።

የተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንዳሉት በከተሞችና በኢንዱስትሪ መስፋፋት ምክንያት ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ተፈጥሯል።


ለፍላጎቱ ምላሽ ለመስጠት ከአዳዲስ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታዎች በተጨማሪ በነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ፣ የማስፋፊያ እና ማዘመን ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝም አመልክተዋል።

የማከፋፈያ ጣቢያዎች ዕድሜ፣ የኃይል ጭነት ከመጠን በላይ መሆን እና በጣቢያዎች ላይ በሚከሰቱ ድንገተኛ ችግሮች በዕቃዎች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ለአቅም ማሳደግ እና ማሻሻያ ሥራዎች መከናወን ምክንያት መሆናቸው ተገልጿል።

እንደ አቶ ጋሻው ገለጻ ባለፉት አምስት ዓመታት በነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 22 የኃይል ትራንስፎርመሮችን በመትከል 310 ሜጋ ዋት ተጨማሪ ኃይል ማግኘት ተችሏል።


ቦሌ ለሚ፣ ሻሸመኔ፣ ጂግጂጋ፣ በደሌ፣ ሐረር ሁለት እና ሶስት፣ ወልቂጤ፣ ደብረ ታቦር፣ ጊንጪ፣ ደብረ ብርሃን፣ ድሬዳዋ ሁለት እና ሶስት፣ አሸጎዳ፣ ገላን፣ ሆሳዕና፣ ባህርዳር ሁለት፣ ጌዶ እና ጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአቅም ማሳደግ፣ ማስፋፊያ እና የማዘመን ሥራዎች ከተከናወኑባቸው መካከል ተጠቃሾች ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025