አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት አምስት ዓመታት በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በተከናወኑ የማስፋፊያ ስራዎች ተጨማሪ 310 ሜጋ ዋት ኃይል ማግኘት መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል አስታወቀ።
የተቋሙ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንዳሉት በከተሞችና በኢንዱስትሪ መስፋፋት ምክንያት ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ተፈጥሯል።
ለፍላጎቱ ምላሽ ለመስጠት ከአዳዲስ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታዎች በተጨማሪ በነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ፣ የማስፋፊያ እና ማዘመን ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝም አመልክተዋል።
የማከፋፈያ ጣቢያዎች ዕድሜ፣ የኃይል ጭነት ከመጠን በላይ መሆን እና በጣቢያዎች ላይ በሚከሰቱ ድንገተኛ ችግሮች በዕቃዎች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ለአቅም ማሳደግ እና ማሻሻያ ሥራዎች መከናወን ምክንያት መሆናቸው ተገልጿል።
እንደ አቶ ጋሻው ገለጻ ባለፉት አምስት ዓመታት በነባር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 22 የኃይል ትራንስፎርመሮችን በመትከል 310 ሜጋ ዋት ተጨማሪ ኃይል ማግኘት ተችሏል።
ቦሌ ለሚ፣ ሻሸመኔ፣ ጂግጂጋ፣ በደሌ፣ ሐረር ሁለት እና ሶስት፣ ወልቂጤ፣ ደብረ ታቦር፣ ጊንጪ፣ ደብረ ብርሃን፣ ድሬዳዋ ሁለት እና ሶስት፣ አሸጎዳ፣ ገላን፣ ሆሳዕና፣ ባህርዳር ሁለት፣ ጌዶ እና ጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአቅም ማሳደግ፣ ማስፋፊያ እና የማዘመን ሥራዎች ከተከናወኑባቸው መካከል ተጠቃሾች ናቸው።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025