
ጎንደር፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል እየሰፈነ የመጣው ሰላም የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በቀሪ ወራት ለመሰብሰብ የታቀደውን ግብር ለማሳካት ሁሉን አቀፍ ጥረት እንደሚደረግ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
የጎንደር ከተማ ገቢዎች መምሪያ ለገቢ ሰብሳቢ ሠራተኞች፣ለአጋር እና ባለድርሻ አካላት ያዘጋጀው የግብር ንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የቢሮው ሃላፊው አቶ ክብረት መሃመድ እንደገለጹት፥ በአሁኑ ወቅት በክልሉ የሰፈነው ሰላም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ ለልማትና ለሰላም ሥራዎች ለማዋል የሚያስችል ነው።
በዚህም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ለክልሉ ገቢ አሰባሰብ ዕቅድ መሳካት በጋራ ሊረባረቡና ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል።
በክልሉ በበጀት ዓመቱ 71 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ግብርና ታክስ ለመሰብሰብ ታቅዶ ባለፋት ስምንት ወራት ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል።
የተሰበሰበው ገቢም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ብልጫ እንዳለው ጠቁመው፣ በክልሉ እየተሻሻለ የመጣው ሰላም ለብልጫው አንድ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰዋል።
በቀሪ ወራት ዕቅዱን ለማሳካት የአመራሩና የግብር ሰብሳቢ ባለሙያዎች የተቀናጀ ጥረትና ርብርብ ወሳኝ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ግብር ለሀገር ልማትና እድገት ቁልፍ ሚና የሚጫወትና ለህዝብም የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማ የልማት ጉዞ የሚፋጠነው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ መሰብሰብ ሲቻል ነው ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው ናቸው።
በከተማው የልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ያሉት በግብር በተሰበሰበ ገቢ መሆኑን ጠቁመው፣በየደረጃው ያለው አመራር ለግብር አሰባሰብ ሥራው ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
የጎንደር ከተማ ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ጥሩዬ አታክልት በበኩላቸው፥በበጀት ዓመቱ በከተማው ከ3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አውስተዋል።
ባለፋት ሰባት ወራት ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ ለልማትና ለሰላም ሥራዎች እንዲውል መደረጉንም ጠቁመዋል።
በንቅናቄ መድረኩ ላይ የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የከተማው የገቢ ሰብሳቢ ባለሙያዎችና አጋር አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026