
ጎንደር፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል እየሰፈነ የመጣው ሰላም የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በቀሪ ወራት ለመሰብሰብ የታቀደውን ግብር ለማሳካት ሁሉን አቀፍ ጥረት እንደሚደረግ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
የጎንደር ከተማ ገቢዎች መምሪያ ለገቢ ሰብሳቢ ሠራተኞች፣ለአጋር እና ባለድርሻ አካላት ያዘጋጀው የግብር ንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የቢሮው ሃላፊው አቶ ክብረት መሃመድ እንደገለጹት፥ በአሁኑ ወቅት በክልሉ የሰፈነው ሰላም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ ለልማትና ለሰላም ሥራዎች ለማዋል የሚያስችል ነው።
በዚህም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ለክልሉ ገቢ አሰባሰብ ዕቅድ መሳካት በጋራ ሊረባረቡና ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል።
በክልሉ በበጀት ዓመቱ 71 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ግብርና ታክስ ለመሰብሰብ ታቅዶ ባለፋት ስምንት ወራት ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል።
የተሰበሰበው ገቢም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ብልጫ እንዳለው ጠቁመው፣ በክልሉ እየተሻሻለ የመጣው ሰላም ለብልጫው አንድ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰዋል።
በቀሪ ወራት ዕቅዱን ለማሳካት የአመራሩና የግብር ሰብሳቢ ባለሙያዎች የተቀናጀ ጥረትና ርብርብ ወሳኝ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ግብር ለሀገር ልማትና እድገት ቁልፍ ሚና የሚጫወትና ለህዝብም የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማ የልማት ጉዞ የሚፋጠነው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ መሰብሰብ ሲቻል ነው ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው ናቸው።
በከተማው የልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ያሉት በግብር በተሰበሰበ ገቢ መሆኑን ጠቁመው፣በየደረጃው ያለው አመራር ለግብር አሰባሰብ ሥራው ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
የጎንደር ከተማ ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ጥሩዬ አታክልት በበኩላቸው፥በበጀት ዓመቱ በከተማው ከ3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አውስተዋል።
ባለፋት ሰባት ወራት ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ ለልማትና ለሰላም ሥራዎች እንዲውል መደረጉንም ጠቁመዋል።
በንቅናቄ መድረኩ ላይ የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የከተማው የገቢ ሰብሳቢ ባለሙያዎችና አጋር አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026