
ጎንደር፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል እየሰፈነ የመጣው ሰላም የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በቀሪ ወራት ለመሰብሰብ የታቀደውን ግብር ለማሳካት ሁሉን አቀፍ ጥረት እንደሚደረግ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
የጎንደር ከተማ ገቢዎች መምሪያ ለገቢ ሰብሳቢ ሠራተኞች፣ለአጋር እና ባለድርሻ አካላት ያዘጋጀው የግብር ንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የቢሮው ሃላፊው አቶ ክብረት መሃመድ እንደገለጹት፥ በአሁኑ ወቅት በክልሉ የሰፈነው ሰላም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ ለልማትና ለሰላም ሥራዎች ለማዋል የሚያስችል ነው።
በዚህም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ለክልሉ ገቢ አሰባሰብ ዕቅድ መሳካት በጋራ ሊረባረቡና ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል።
በክልሉ በበጀት ዓመቱ 71 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ግብርና ታክስ ለመሰብሰብ ታቅዶ ባለፋት ስምንት ወራት ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል።
የተሰበሰበው ገቢም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ብልጫ እንዳለው ጠቁመው፣ በክልሉ እየተሻሻለ የመጣው ሰላም ለብልጫው አንድ ምክንያት መሆኑን ጠቅሰዋል።
በቀሪ ወራት ዕቅዱን ለማሳካት የአመራሩና የግብር ሰብሳቢ ባለሙያዎች የተቀናጀ ጥረትና ርብርብ ወሳኝ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ግብር ለሀገር ልማትና እድገት ቁልፍ ሚና የሚጫወትና ለህዝብም የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማ የልማት ጉዞ የሚፋጠነው ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ መሰብሰብ ሲቻል ነው ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው ናቸው።
በከተማው የልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ያሉት በግብር በተሰበሰበ ገቢ መሆኑን ጠቁመው፣በየደረጃው ያለው አመራር ለግብር አሰባሰብ ሥራው ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
የጎንደር ከተማ ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ጥሩዬ አታክልት በበኩላቸው፥በበጀት ዓመቱ በከተማው ከ3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አውስተዋል።
ባለፋት ሰባት ወራት ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ ለልማትና ለሰላም ሥራዎች እንዲውል መደረጉንም ጠቁመዋል።
በንቅናቄ መድረኩ ላይ የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የከተማው የገቢ ሰብሳቢ ባለሙያዎችና አጋር አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026