አዲስ አበባ፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦የኦዲት ባለሙያዎች በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ሙያዊ እውቀታቸውንና የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውን ማሳደግ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ገለፀ።
የውጭ ኦዲተሮች ማህበር ያዘጋጀው በኦዲትና በፋይናንስ ሪፖርት ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የተመሰከረላቸው ሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የተሳተፉ ሲሆን በዘርፉ አለም የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ስርዓቶች በተመለከተ ማብራሪያም ተሰጥቷል።
በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ተጠባባቂ ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ አጎናፍር እንዳሉት፥ ቦርዱ በዘርፉ ሙያዊ ስነምግባርና ነፃነትን ለማስጠበቅ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
ቦርዱ ሪፖርት አቅራቢ አካላት ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ የሂሳብ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ለማስቻልና ተጠያቂነትን ለማስፈን እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ባለሙያዎች ተከታታይነት ያለው የሙያ ማጎልበቻ ስልጠናዎችን አግኝተው ተወዳዳሪነታቸውን ለማሻሻልና ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ቦርዱ ፍቃድ የሚሰጥበትን መመሪያ በማሻሻል የፍቃድ አይነቶችን ማሳደጉን ጠቁመው፥ በዳይሬክተሮች ቦርድ ፀድቆ ወደፍትህ ሚኒስቴር የተመራ ደንብ መኖሩንም ተናግረዋል።
ቦርዱ የህዝብን ጥቅም ማስጠበቅን ዓላማው አድርጎ እየሰራ እንደመሆኑ ባለሙያዎች ቴክኖሎጂን ተጠቅመው እውቀትና ክህሎታቸውን እንዲያሻሽሉ የክትትልና ቁጥጥር ስራ እንደሚሰራም ገልፀዋል።
ባለሙያዎች ቴክኖሎጂን የመጠቀም አቅማቸውን በማሳደግ ተወዳዳሪ ሆነው መቀጠል እንዳለባቸውም ነው ያስረዱት።
የውጭ ኦዲተሮች ማህበር ፕሬዝዳንት ዳንኤል ጌታነህ በበኩላቸው፥ ማህበሩ የኦዲት ድርጅት ያላቸው ከ130 በላይ አባላት እንዳሉት ተናግረዋል።
በፋይናንስ ሪፖርት ላይ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ስርዓቶች ትግበራ እንዳለ አንስተው፥ በኦዲት ዘርፍ የቴክኖሎጂ ስርዓቶችን ለማስፋት ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል።
በውጭ ያሉ ሶፍትዌሮች ላይ ግንዛቤ ከማስጨበጥ ባለፈ ቴክኖሎጂ የማበልፀግ ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል።
የኦዲት ሪፖርት ተዓማኒና ትክክለኛ እንዲሆን ለማስቻል ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ በመሆኑ ባለሞያዎች ቴክኖሎጂን በመጠቀም የፋይናንስ ስርዓቱን እንዲያዘምኑ ጠይቀዋል።
የዛሬው መድረክ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ መሆኑንና በቀጣይም መሰል ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።
በመድረኩ የተሳተፉት የተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያ ዘቢባ አሊና የተመሰከረላቸው የኦዲት ባለሙያ ሀብታሙ ተስፋዬ በበኩላቸው በተለይ በኦዲት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ የተጀመሩ ስራዎች ቢኖሩም መጠናከር እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ውይይቱ ስራቸውን ለማዘመን የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን እንዲገነዘቡ የሚያግዝ እንደሆነም ጠቁመዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025