የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኦዲት ባለሙያዎች በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ሙያዊ እውቀታቸውን ማሳደግ አለባቸው

Mar 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦የኦዲት ባለሙያዎች በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን ሙያዊ እውቀታቸውንና የቴክኖሎጂ አጠቃቀማቸውን ማሳደግ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ገለፀ።


የውጭ ኦዲተሮች ማህበር ያዘጋጀው በኦዲትና በፋይናንስ ሪፖርት ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።


በመድረኩ የተመሰከረላቸው ሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የተሳተፉ ሲሆን በዘርፉ አለም የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ስርዓቶች በተመለከተ ማብራሪያም ተሰጥቷል።


በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ተጠባባቂ ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ አጎናፍር እንዳሉት፥ ቦርዱ በዘርፉ ሙያዊ ስነምግባርና ነፃነትን ለማስጠበቅ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።


ቦርዱ ሪፖርት አቅራቢ አካላት ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ የሂሳብ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ለማስቻልና ተጠያቂነትን ለማስፈን እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።


ባለሙያዎች ተከታታይነት ያለው የሙያ ማጎልበቻ ስልጠናዎችን አግኝተው ተወዳዳሪነታቸውን ለማሻሻልና ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።


ቦርዱ ፍቃድ የሚሰጥበትን መመሪያ በማሻሻል የፍቃድ አይነቶችን ማሳደጉን ጠቁመው፥ በዳይሬክተሮች ቦርድ ፀድቆ ወደፍትህ ሚኒስቴር የተመራ ደንብ መኖሩንም ተናግረዋል።


ቦርዱ የህዝብን ጥቅም ማስጠበቅን ዓላማው አድርጎ እየሰራ እንደመሆኑ ባለሙያዎች ቴክኖሎጂን ተጠቅመው እውቀትና ክህሎታቸውን እንዲያሻሽሉ የክትትልና ቁጥጥር ስራ እንደሚሰራም ገልፀዋል።


ባለሙያዎች ቴክኖሎጂን የመጠቀም አቅማቸውን በማሳደግ ተወዳዳሪ ሆነው መቀጠል እንዳለባቸውም ነው ያስረዱት።


የውጭ ኦዲተሮች ማህበር ፕሬዝዳንት ዳንኤል ጌታነህ በበኩላቸው፥ ማህበሩ የኦዲት ድርጅት ያላቸው ከ130 በላይ አባላት እንዳሉት ተናግረዋል።


በፋይናንስ ሪፖርት ላይ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ስርዓቶች ትግበራ እንዳለ አንስተው፥ በኦዲት ዘርፍ የቴክኖሎጂ ስርዓቶችን ለማስፋት ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል።


በውጭ ያሉ ሶፍትዌሮች ላይ ግንዛቤ ከማስጨበጥ ባለፈ ቴክኖሎጂ የማበልፀግ ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል።


የኦዲት ሪፖርት ተዓማኒና ትክክለኛ እንዲሆን ለማስቻል ቴክኖሎጂን መጠቀም አስፈላጊ በመሆኑ ባለሞያዎች ቴክኖሎጂን በመጠቀም የፋይናንስ ስርዓቱን እንዲያዘምኑ ጠይቀዋል።


የዛሬው መድረክ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ መሆኑንና በቀጣይም መሰል ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።


በመድረኩ የተሳተፉት የተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያ ዘቢባ አሊና የተመሰከረላቸው የኦዲት ባለሙያ ሀብታሙ ተስፋዬ በበኩላቸው በተለይ በኦዲት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ የተጀመሩ ስራዎች ቢኖሩም መጠናከር እንዳለባቸው ተናግረዋል።


ውይይቱ ስራቸውን ለማዘመን የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን እንዲገነዘቡ የሚያግዝ እንደሆነም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026