
ባሕር ዳር፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ የመስኖ ፕሮጀክቶችን የማስፋፋት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ አየልኝ መሳፍንት ለኢዜአ እንዳሉት፤ አርሶ አደሩ ከዝናብ ጠባቂነት ተላቆ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም ዓመቱን ሙሉ እንዲያለማ በዘመናዊ መስኖ ልማት ተጠቃሚ እየተደረገ ነው።
በተያዘው በጀት ዓመት ከ23 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ማልማት የሚያስችሉ 154 መካከለኛና አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ታቅዶ 67 ፕሮጀክቶችን ወደ ግንባታ ማስገባት መቻሉን ጠ

ቅሰዋል።
ከነዚህም መካከል አራት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ልማት መግባታቸውን አንስተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት ሲበቁ ከ53 ሽህ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ብለዋል።
ሌሎች 17 የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ከተቋራጮች ጋር ውል በመፈጸም መስጠቱን አመልክተው፤ የታቀደውን ለማሳካት ከወዲሁ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ከነባሮቹ በተጨማሪ እየተከናወነ ያለው የመስኖ ፕሮጀክቶችን የማስፋፋት ተግባር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም ቀጣይ ወደ ግንባታ የሚገቡ የ110 ፕሮጀክቶች የጥናትና ዲዛይን ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ መልማት እንደሚችል ጠቅሰው፤ እስካሁን ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
ቀሪውም ለማልማት ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች የማስፋፋቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አመልክቷል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026