
ባሕር ዳር፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ የመስኖ ፕሮጀክቶችን የማስፋፋት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ አየልኝ መሳፍንት ለኢዜአ እንዳሉት፤ አርሶ አደሩ ከዝናብ ጠባቂነት ተላቆ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም ዓመቱን ሙሉ እንዲያለማ በዘመናዊ መስኖ ልማት ተጠቃሚ እየተደረገ ነው።
በተያዘው በጀት ዓመት ከ23 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ማልማት የሚያስችሉ 154 መካከለኛና አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ታቅዶ 67 ፕሮጀክቶችን ወደ ግንባታ ማስገባት መቻሉን ጠ

ቅሰዋል።
ከነዚህም መካከል አራት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ልማት መግባታቸውን አንስተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት ሲበቁ ከ53 ሽህ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ብለዋል።
ሌሎች 17 የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ከተቋራጮች ጋር ውል በመፈጸም መስጠቱን አመልክተው፤ የታቀደውን ለማሳካት ከወዲሁ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ከነባሮቹ በተጨማሪ እየተከናወነ ያለው የመስኖ ፕሮጀክቶችን የማስፋፋት ተግባር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም ቀጣይ ወደ ግንባታ የሚገቡ የ110 ፕሮጀክቶች የጥናትና ዲዛይን ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ መልማት እንደሚችል ጠቅሰው፤ እስካሁን ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
ቀሪውም ለማልማት ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች የማስፋፋቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አመልክቷል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026