
ባሕር ዳር፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ የመስኖ ፕሮጀክቶችን የማስፋፋት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ አየልኝ መሳፍንት ለኢዜአ እንዳሉት፤ አርሶ አደሩ ከዝናብ ጠባቂነት ተላቆ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም ዓመቱን ሙሉ እንዲያለማ በዘመናዊ መስኖ ልማት ተጠቃሚ እየተደረገ ነው።
በተያዘው በጀት ዓመት ከ23 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ማልማት የሚያስችሉ 154 መካከለኛና አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ታቅዶ 67 ፕሮጀክቶችን ወደ ግንባታ ማስገባት መቻሉን ጠ

ቅሰዋል።
ከነዚህም መካከል አራት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ልማት መግባታቸውን አንስተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት ሲበቁ ከ53 ሽህ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ብለዋል።
ሌሎች 17 የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ከተቋራጮች ጋር ውል በመፈጸም መስጠቱን አመልክተው፤ የታቀደውን ለማሳካት ከወዲሁ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ከነባሮቹ በተጨማሪ እየተከናወነ ያለው የመስኖ ፕሮጀክቶችን የማስፋፋት ተግባር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም ቀጣይ ወደ ግንባታ የሚገቡ የ110 ፕሮጀክቶች የጥናትና ዲዛይን ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ መልማት እንደሚችል ጠቅሰው፤ እስካሁን ጥቅም ላይ የዋለው 10 በመቶ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
ቀሪውም ለማልማት ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች የማስፋፋቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አመልክቷል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026