
ደብረ ብርሀን፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ በሚሰሩ ስራዎች የድርሻውን እንደሚወጣ አስታውቋል።
በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የ2ኛ እና የ1ኛ ደረጃ ተማሪዎች የጥናትና ምርምር የፈጠራ ስራዎች የማቅረብና የስፖርታዊ ውድድር ዛሬ ተጀምሯል።

የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ እንዳሉት ተማሪዎች ከቀለም ትምህርት ባሻገር የፈጠራ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር ይገባል።
ለዚህም ተማሪዎችን ከታች ጀምሮ በዝንባሌያቸው መሰረት እገዛ በማድረግ በጥናትና ምርምር እውቀትና ክህሎታቸውን አውጥተው እንዲጠቀሙ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
የተማሪዎች የፈጠራ ስራ ቴክኖሎጂን ከሌሎች በመቅዳት ከማላመድ ባሻገር አዳዲስ ግኝቶች ላይ በማተኮር ለሀገራችን ብልጽግና የቀጣይ መሰረት መሆን እንዳለባቸው አስረድተዋል።
የከተማ አስተዳደሩም የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ በሚሰሩ ስራዎች የበኩሉን ድርሻ ይወጣል ነው ያሉት።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መቅደስ ብዙነህ በበኩላቸው ውድድሩ ተማሪዎችን በምርምርና በስልጠና በማገዝ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለመቅረጽ ያለመ ውድድር ነው ብለዋል።
በውድድሩ የግብርና ስራን የሚደግፉ የድሮን ቴክኖሎጂ የቱሪዝም ሀብትን የሚያስተዋውቁ እና ኢንቨስትመንትን የሚደግፉ 40 የፈጠራ ስራዎች በተማሪዎቹ መቅረባቸውን ገልፀዋል።

የሃይለማሪያም ማሞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ9ኛ ክፍል ተማሪ ሳሙኤል ዓለማየሁ እንዳለው በተለይ የአየር ብክለትን የሚከላከል ቴክኖሎጂ ለውድድር ይዞ ቀርቧል።
ተማሪ እንደሻው ይታገሱ በበኩሉ የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ለሀገር ጥቅም እንዲውሉ ዩኒቨርስቲዎችና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ሊደግፉ እንደሚገባም ጠይቋል።
ይኸው የጥናትና ምርምር የፈጠራ ስራ እና ስፖርታዊ ውድድር ከመጋቢት 5 እስከ 7/2017 ዓም እንደሚቆይም ታውቋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026