የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አስተዳደሩ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ በሚሰሩ ስራዎች የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ገለፀ

Mar 15, 2025

IDOPRESS

ደብረ ብርሀን፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ በሚሰሩ ስራዎች የድርሻውን እንደሚወጣ አስታውቋል።

በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የ2ኛ እና የ1ኛ ደረጃ ተማሪዎች የጥናትና ምርምር የፈጠራ ስራዎች የማቅረብና የስፖርታዊ ውድድር ዛሬ ተጀምሯል።


የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ እንዳሉት ተማሪዎች ከቀለም ትምህርት ባሻገር የፈጠራ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር ይገባል።

ለዚህም ተማሪዎችን ከታች ጀምሮ በዝንባሌያቸው መሰረት እገዛ በማድረግ በጥናትና ምርምር እውቀትና ክህሎታቸውን አውጥተው እንዲጠቀሙ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የተማሪዎች የፈጠራ ስራ ቴክኖሎጂን ከሌሎች በመቅዳት ከማላመድ ባሻገር አዳዲስ ግኝቶች ላይ በማተኮር ለሀገራችን ብልጽግና የቀጣይ መሰረት መሆን እንዳለባቸው አስረድተዋል።

የከተማ አስተዳደሩም የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ በሚሰሩ ስራዎች የበኩሉን ድርሻ ይወጣል ነው ያሉት።


የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መቅደስ ብዙነህ በበኩላቸው ውድድሩ ተማሪዎችን በምርምርና በስልጠና በማገዝ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለመቅረጽ ያለመ ውድድር ነው ብለዋል።

በውድድሩ የግብርና ስራን የሚደግፉ የድሮን ቴክኖሎጂ የቱሪዝም ሀብትን የሚያስተዋውቁ እና ኢንቨስትመንትን የሚደግፉ 40 የፈጠራ ስራዎች በተማሪዎቹ መቅረባቸውን ገልፀዋል።


የሃይለማሪያም ማሞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ9ኛ ክፍል ተማሪ ሳሙኤል ዓለማየሁ እንዳለው በተለይ የአየር ብክለትን የሚከላከል ቴክኖሎጂ ለውድድር ይዞ ቀርቧል።

ተማሪ እንደሻው ይታገሱ በበኩሉ የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ለሀገር ጥቅም እንዲውሉ ዩኒቨርስቲዎችና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ሊደግፉ እንደሚገባም ጠይቋል።

ይኸው የጥናትና ምርምር የፈጠራ ስራ እና ስፖርታዊ ውድድር ከመጋቢት 5 እስከ 7/2017 ዓም እንደሚቆይም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026