ደብረ ብርሀን፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ በሚሰሩ ስራዎች የድርሻውን እንደሚወጣ አስታውቋል።
በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የ2ኛ እና የ1ኛ ደረጃ ተማሪዎች የጥናትና ምርምር የፈጠራ ስራዎች የማቅረብና የስፖርታዊ ውድድር ዛሬ ተጀምሯል።
የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ እንዳሉት ተማሪዎች ከቀለም ትምህርት ባሻገር የፈጠራ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር ይገባል።
ለዚህም ተማሪዎችን ከታች ጀምሮ በዝንባሌያቸው መሰረት እገዛ በማድረግ በጥናትና ምርምር እውቀትና ክህሎታቸውን አውጥተው እንዲጠቀሙ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
የተማሪዎች የፈጠራ ስራ ቴክኖሎጂን ከሌሎች በመቅዳት ከማላመድ ባሻገር አዳዲስ ግኝቶች ላይ በማተኮር ለሀገራችን ብልጽግና የቀጣይ መሰረት መሆን እንዳለባቸው አስረድተዋል።
የከተማ አስተዳደሩም የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ በሚሰሩ ስራዎች የበኩሉን ድርሻ ይወጣል ነው ያሉት።
የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መቅደስ ብዙነህ በበኩላቸው ውድድሩ ተማሪዎችን በምርምርና በስልጠና በማገዝ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለመቅረጽ ያለመ ውድድር ነው ብለዋል።
በውድድሩ የግብርና ስራን የሚደግፉ የድሮን ቴክኖሎጂ የቱሪዝም ሀብትን የሚያስተዋውቁ እና ኢንቨስትመንትን የሚደግፉ 40 የፈጠራ ስራዎች በተማሪዎቹ መቅረባቸውን ገልፀዋል።
የሃይለማሪያም ማሞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ9ኛ ክፍል ተማሪ ሳሙኤል ዓለማየሁ እንዳለው በተለይ የአየር ብክለትን የሚከላከል ቴክኖሎጂ ለውድድር ይዞ ቀርቧል።
ተማሪ እንደሻው ይታገሱ በበኩሉ የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ለሀገር ጥቅም እንዲውሉ ዩኒቨርስቲዎችና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ሊደግፉ እንደሚገባም ጠይቋል።
ይኸው የጥናትና ምርምር የፈጠራ ስራ እና ስፖርታዊ ውድድር ከመጋቢት 5 እስከ 7/2017 ዓም እንደሚቆይም ታውቋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025