
ባህርዳር፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- በሀገራችን ምርታማነትን በማሳደግ አገልግሎትን የሚያቀላጥፉ የፈጠራ ስራዎችን ለማዳበር በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለፀ።
የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ የስልጠናና የስታርታፕ ውድድር መዝጊያ መርሃ ግብር በባህርዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በሀገሪቱ ምርታማነትን የሚያሳደጉና አገልግሎትን የሚያቀላጥፉ የፈጠራ ስራዎችን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በሁሉም ዘርፍ የመንግስትንና የህዝብን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ቴክኖሎጂ በመፍጠር ጠንካራ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሚናው የጎላ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሚኒስቴሩ በወጣቶች የሚከናወኑ የፈጠራ ስራዎች(ስታርታፕ) አቅም እንዲጎለብት ተከታታይ ውድድሮችንና ስልጠናዎችን በመስጠት የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ይህን ተግባር ለማሳካትም ከዩኒቨርሲቲዎችና ከክልል ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

በእለቱም የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አዲሱን ሎጎና ሌሎች የአሰራር ሂደቶችን የማስተዋወቅ ስራ እንደሰራም ተመልክቷል።
በመድረኩም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደን ጨምሮ ሌሎች የሚኒስቴሩ ኃላፊዎችና የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026