
ባህርዳር፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- በሀገራችን ምርታማነትን በማሳደግ አገልግሎትን የሚያቀላጥፉ የፈጠራ ስራዎችን ለማዳበር በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለፀ።
የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ የስልጠናና የስታርታፕ ውድድር መዝጊያ መርሃ ግብር በባህርዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በሀገሪቱ ምርታማነትን የሚያሳደጉና አገልግሎትን የሚያቀላጥፉ የፈጠራ ስራዎችን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በሁሉም ዘርፍ የመንግስትንና የህዝብን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ቴክኖሎጂ በመፍጠር ጠንካራ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሚናው የጎላ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሚኒስቴሩ በወጣቶች የሚከናወኑ የፈጠራ ስራዎች(ስታርታፕ) አቅም እንዲጎለብት ተከታታይ ውድድሮችንና ስልጠናዎችን በመስጠት የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ይህን ተግባር ለማሳካትም ከዩኒቨርሲቲዎችና ከክልል ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

በእለቱም የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አዲሱን ሎጎና ሌሎች የአሰራር ሂደቶችን የማስተዋወቅ ስራ እንደሰራም ተመልክቷል።
በመድረኩም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደን ጨምሮ ሌሎች የሚኒስቴሩ ኃላፊዎችና የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026