የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ምርታማነትን በማሳደግ አገልግሎትን የሚያቀላጥፉ የፈጠራ ስራዎችን ለማዳበር ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ ነው - የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- በሀገራችን ምርታማነትን በማሳደግ አገልግሎትን የሚያቀላጥፉ የፈጠራ ስራዎችን ለማዳበር በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለፀ።

የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ የስልጠናና የስታርታፕ ውድድር መዝጊያ መርሃ ግብር በባህርዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በሀገሪቱ ምርታማነትን የሚያሳደጉና አገልግሎትን የሚያቀላጥፉ የፈጠራ ስራዎችን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።


በሁሉም ዘርፍ የመንግስትንና የህዝብን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ቴክኖሎጂ በመፍጠር ጠንካራ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሚናው የጎላ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ሚኒስቴሩ በወጣቶች የሚከናወኑ የፈጠራ ስራዎች(ስታርታፕ) አቅም እንዲጎለብት ተከታታይ ውድድሮችንና ስልጠናዎችን በመስጠት የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ይህን ተግባር ለማሳካትም ከዩኒቨርሲቲዎችና ከክልል ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።


በእለቱም የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አዲሱን ሎጎና ሌሎች የአሰራር ሂደቶችን የማስተዋወቅ ስራ እንደሰራም ተመልክቷል።

በመድረኩም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደን ጨምሮ ሌሎች የሚኒስቴሩ ኃላፊዎችና የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025