
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፡- በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ሎሚ በዶ የተመራ ቡድን በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜና ቦራ ወረዳዎች የተሰሩና አየተሰሩ ያሉ የልማት ሥራዎች የመስክ ጉብኝት አድርጓል።
በጉብኝቱ ከምክትል አፈ ጉባኤዋ በተጨማሪ የምሥራቅ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ እና ሌሎች ከዞኑ የተወከሉ የምክር ቤት አባላት መሳተፋቸውን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ጉብኝቱ በዞኑ ሉሜ እና ቦራ ወረዳዎች የተሰሩ እና በመሰራት ላይ የሚገኙ የበጋ ስንዴ እና የሙዝ ክላስተር የግብርና ኢንሼቲቮች እና አዲሱን የገጠር ቀበሌዎች አደረጃጀት ጽህፈት ቤቶችን የስራ እንቅስቃሴ ያካተተ ነው።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላቱ ከጉብኝታቸው በኋላ የሕዝብ ውክልና የመስክ ሥራ ግብረ-መልስ መስጠታቸውም ተገልጿል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026