የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ ቡና ዓለም አቀፍ ተቀባይነቱ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል

Mar 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ቡና ቻይናን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነቱ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ደዋኖ ከድር ገለጹ።

በቤጂንግ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሶስተኛዉ "Beijing CBD International Coffee Culture Festival" ላይ ተሳትፎ አድርጓል፡፡

ፕሮግራሙ የተካሄደው ”The World’s Coffee Heritage-The Light of Ethiopia-The Cradle of Coffee Culture” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።

በቻይና የንግድ ሚኒስቴር የሰሪኩሌሽን ኢንዱስትሪ ፕሮሞሽን እና የኢትዮጵያ ሚሲዮን ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል።


በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ደዋኖ ከድር የኢትዮጵን ቡና አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

በገለጻቸውም ኢትዮጵያ የጥሩ ጣዕም(አረቢካ) ቡና መገኛ፣ ጥራት ያለው ቡና አምራች እና ላኪ እንዲሁም የጥሩ ጣዕም እና የተለያዩ ባህሪያት ያላቸዉ በርካታ የቡና ዝርያዎች ባለቤት ናት ብለዋል።

የኢትዮጵያ ቡና ፍላጎት የቻይና ገበያን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን አመልክተዋል።

በተጨማሪም በመንግስት በኩል የቡናን አመራረት እና ጥራት ለማሳደግ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

መንግስት በሰጠው ትኩረት በኢትዮጵያ የቡና ምርት በብዛት እና በጥራት እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ከቻይና ኩባንያዎች ጋር በቡና ወጪ ንግድ እና በሌሎች የቡና ዘርፎች ላይ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ለዚህም ሚሲዮኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው አምባሳደሩ የገለጹት።

በፌስቲቫሉ የተለያዩ የኢትዮጵያ የቡና ወጪ ምርቶች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን በቡና ንግድ ዙሪያ ከተለያዩ ኩባንያ ተወካዮች ጋር ውይይቶች ተደርጓል።

በፕሮግራሙ ላይ ኩባንያዎች፣ የተለያዩ ቡና ገዢዎች፣ ላኪዎች፣ አከፋፋዮች፣ አቀነባሪዎች እና በቡና ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የመንግስት እና የግል ተቋማት መሳተፋቸውን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026