የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ ቡና ዓለም አቀፍ ተቀባይነቱ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል

Mar 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ቡና ቻይናን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነቱ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ደዋኖ ከድር ገለጹ።

በቤጂንግ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሶስተኛዉ "Beijing CBD International Coffee Culture Festival" ላይ ተሳትፎ አድርጓል፡፡

ፕሮግራሙ የተካሄደው ”The World’s Coffee Heritage-The Light of Ethiopia-The Cradle of Coffee Culture” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።

በቻይና የንግድ ሚኒስቴር የሰሪኩሌሽን ኢንዱስትሪ ፕሮሞሽን እና የኢትዮጵያ ሚሲዮን ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል።


በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ደዋኖ ከድር የኢትዮጵን ቡና አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

በገለጻቸውም ኢትዮጵያ የጥሩ ጣዕም(አረቢካ) ቡና መገኛ፣ ጥራት ያለው ቡና አምራች እና ላኪ እንዲሁም የጥሩ ጣዕም እና የተለያዩ ባህሪያት ያላቸዉ በርካታ የቡና ዝርያዎች ባለቤት ናት ብለዋል።

የኢትዮጵያ ቡና ፍላጎት የቻይና ገበያን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን አመልክተዋል።

በተጨማሪም በመንግስት በኩል የቡናን አመራረት እና ጥራት ለማሳደግ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

መንግስት በሰጠው ትኩረት በኢትዮጵያ የቡና ምርት በብዛት እና በጥራት እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ከቻይና ኩባንያዎች ጋር በቡና ወጪ ንግድ እና በሌሎች የቡና ዘርፎች ላይ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ለዚህም ሚሲዮኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው አምባሳደሩ የገለጹት።

በፌስቲቫሉ የተለያዩ የኢትዮጵያ የቡና ወጪ ምርቶች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን በቡና ንግድ ዙሪያ ከተለያዩ ኩባንያ ተወካዮች ጋር ውይይቶች ተደርጓል።

በፕሮግራሙ ላይ ኩባንያዎች፣ የተለያዩ ቡና ገዢዎች፣ ላኪዎች፣ አከፋፋዮች፣ አቀነባሪዎች እና በቡና ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የመንግስት እና የግል ተቋማት መሳተፋቸውን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026