የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኢትዮጵያ ቡና ዓለም አቀፍ ተቀባይነቱ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል

Mar 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ቡና ቻይናን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነቱ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ደዋኖ ከድር ገለጹ።

በቤጂንግ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሶስተኛዉ "Beijing CBD International Coffee Culture Festival" ላይ ተሳትፎ አድርጓል፡፡

ፕሮግራሙ የተካሄደው ”The World’s Coffee Heritage-The Light of Ethiopia-The Cradle of Coffee Culture” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።

በቻይና የንግድ ሚኒስቴር የሰሪኩሌሽን ኢንዱስትሪ ፕሮሞሽን እና የኢትዮጵያ ሚሲዮን ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተውታል።


በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ደዋኖ ከድር የኢትዮጵን ቡና አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

በገለጻቸውም ኢትዮጵያ የጥሩ ጣዕም(አረቢካ) ቡና መገኛ፣ ጥራት ያለው ቡና አምራች እና ላኪ እንዲሁም የጥሩ ጣዕም እና የተለያዩ ባህሪያት ያላቸዉ በርካታ የቡና ዝርያዎች ባለቤት ናት ብለዋል።

የኢትዮጵያ ቡና ፍላጎት የቻይና ገበያን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን አመልክተዋል።

በተጨማሪም በመንግስት በኩል የቡናን አመራረት እና ጥራት ለማሳደግ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

መንግስት በሰጠው ትኩረት በኢትዮጵያ የቡና ምርት በብዛት እና በጥራት እያደገ መምጣቱንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ከቻይና ኩባንያዎች ጋር በቡና ወጪ ንግድ እና በሌሎች የቡና ዘርፎች ላይ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ለዚህም ሚሲዮኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ነው አምባሳደሩ የገለጹት።

በፌስቲቫሉ የተለያዩ የኢትዮጵያ የቡና ወጪ ምርቶች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን በቡና ንግድ ዙሪያ ከተለያዩ ኩባንያ ተወካዮች ጋር ውይይቶች ተደርጓል።

በፕሮግራሙ ላይ ኩባንያዎች፣ የተለያዩ ቡና ገዢዎች፣ ላኪዎች፣ አከፋፋዮች፣ አቀነባሪዎች እና በቡና ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የመንግስት እና የግል ተቋማት መሳተፋቸውን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025