የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የአሽከርካሪዎች የብቃት ምዘና ሊካሄድ ነው

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ በህዝብ እና በጭነት አገልግሎት የተሰማሩ የንግድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎችን ብቃት መለካት የሚያስችል ሰነድ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን ገለጹ።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን የብቃት ምዘናውን ካበለፀገው ኤስዲኤስ ከተሰኘው ተቋም አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።


የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር የአሽከርካሪዎችን ብቃት ለመመዘን ዝግጅት እያደረገ ነው።

ሚኒስትር ዴኤታው የትራፊክ አደጋን ተከላክሎ በማሽከርከር በሰው እና በንብረት ላይ የሚደርሰውን ውድመት ለመከላከል ለሚደረገው ርብርብ ከሰነዶች ዝግጅት ባሻገር ወደ ተግባር ሲገባ አሰራሩን ተፈፃሚ ለማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቀጣይ ውይይቶች እንደሚደረጉም ገልጸዋል።

የብቃት ምዘናው በየደረጃው ተከፋፍሎ ይሰጣል።

በመጀመሪያ ዙር የአገር አቋራጭ አውቶቡሶችንና የድንበር ተሻገሪ የጭነት ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎችን ብቃት መለካት የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025