የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የአሽከርካሪዎች የብቃት ምዘና ሊካሄድ ነው

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ በህዝብ እና በጭነት አገልግሎት የተሰማሩ የንግድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎችን ብቃት መለካት የሚያስችል ሰነድ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን ገለጹ።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን የብቃት ምዘናውን ካበለፀገው ኤስዲኤስ ከተሰኘው ተቋም አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።


የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር የአሽከርካሪዎችን ብቃት ለመመዘን ዝግጅት እያደረገ ነው።

ሚኒስትር ዴኤታው የትራፊክ አደጋን ተከላክሎ በማሽከርከር በሰው እና በንብረት ላይ የሚደርሰውን ውድመት ለመከላከል ለሚደረገው ርብርብ ከሰነዶች ዝግጅት ባሻገር ወደ ተግባር ሲገባ አሰራሩን ተፈፃሚ ለማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቀጣይ ውይይቶች እንደሚደረጉም ገልጸዋል።

የብቃት ምዘናው በየደረጃው ተከፋፍሎ ይሰጣል።

በመጀመሪያ ዙር የአገር አቋራጭ አውቶቡሶችንና የድንበር ተሻገሪ የጭነት ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎችን ብቃት መለካት የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026