
አዲስ አበባ ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ በህዝብ እና በጭነት አገልግሎት የተሰማሩ የንግድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎችን ብቃት መለካት የሚያስችል ሰነድ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን ገለጹ።
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን የብቃት ምዘናውን ካበለፀገው ኤስዲኤስ ከተሰኘው ተቋም አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር የአሽከርካሪዎችን ብቃት ለመመዘን ዝግጅት እያደረገ ነው።
ሚኒስትር ዴኤታው የትራፊክ አደጋን ተከላክሎ በማሽከርከር በሰው እና በንብረት ላይ የሚደርሰውን ውድመት ለመከላከል ለሚደረገው ርብርብ ከሰነዶች ዝግጅት ባሻገር ወደ ተግባር ሲገባ አሰራሩን ተፈፃሚ ለማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቀጣይ ውይይቶች እንደሚደረጉም ገልጸዋል።
የብቃት ምዘናው በየደረጃው ተከፋፍሎ ይሰጣል።
በመጀመሪያ ዙር የአገር አቋራጭ አውቶቡሶችንና የድንበር ተሻገሪ የጭነት ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎችን ብቃት መለካት የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026