ቦንጋ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ):-በአካባቢያቸው የተገነቡ የመስኖ አውታሮችን ተጠቅመው ካለሙት ስንዴ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ጨና ወረዳ አርሶ አደሮች ተናገሩ።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶር)ና ሌሎች ከፍተኛ አመራር አባላት በጨና ወረዳ የለማ የበጋ መስኖ ስንዴና የአትክልት ልማትን ጎብኝቷል።
በዚህ ወቅት በወረዳው የቦባ ጎታ ቀበሌ አርሶአደር ገረመዉ ሀይሌ በሰጡት አስተያየት፤ ከዚህ ቀደም በአካባቢያቸው ዘመናዊ የመስኖ አውታር ባለመኖሩ በጋውን ለምርት እንደማይጠቀሙ አስታውሰዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአካባቢያቸው የተገነቡ ዘመናዊ የመስኖ አውታሮችን ተጠቅመው ለመጀመሪያ ጊዜ የበጋ መስኖ ስንዴ ያለሙ መሆኑን ገልጸው፤ አሁን ላይ የምርቱ ቁመናው ጥሩ እንደሆነና የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁም ተናግረዋል።
ሌላኛው አርሶ አደር ወጣት ፍቅሬ በቀለ በበኩሉ፤ ግማሽ ሄክታር ማሳ ላይ ስንዴ ማልማቱን ገልጿል።
በበጋው ወቅት ብዙም ውጤት በማይሰጡ የእርሻ ስራዎች ያሳልፉ እንደነበር አስታውሶ፤ የመስኖ አውታር ግንባታ ሳቢያ ዉሃ እንደልብ በማግኘት ልማቱን እያከናወኑ እንደሚገኝ ተናግሯል።
አርኦ አደሮቹ እንዳሉት፤ በኩታ ገጠም ማልማታቸው በጋራ የአረም ቁጥጥር ለማድረግ፣ ምርትን በጋራ ለመሰብሰብ እና ተደጋግፎ ለመስራት ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በክልሉ የተገነቡ የመሰኖ ልማት አውታሮች የእርሻ ስራ ውጤታማነት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው።
በተለይም የክልሉ የእርሻ ስራን ስኬታማነት ለማረጋገጥ የውሃ አማራጭን ለመጠቀም መስኖ አውታሮች የማስፋት ስራ ውጤት እያመጣ መሆኑንና ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል ።
አርሶ አደሩ ከዝናብ ጠባቂነት በመላቀቅ የመሬትና የውሃ ሀብቶች በተገቢው ተጠቅሞ የኢኮኖሚ አቅሙን ማጎልበት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በበኩላቸው፤ በክልሉ መስኖን በመጠቀም ስንዴ፣ ሩዝና አትክልትን ጨምሮ ሌሎችንም የማልማቱ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በክልሉ ዘንድሮ በሁለተኛ ዙር መስኖና በበልግ 103 ሺህ ሄክታር ማሳ እየለማ መሆኑን ጠቁመዋል።
ክልሉ ያለውን ፀጋ ወደ ልማት ለመቀየር እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን ናቸው።
አበረታች የልማት ስራዎች የማስፋትና የመደገፍ ስራ ይጠናከራል ነው ያሉት ።
በክልሉ ውስጥ ያሉ ፀጋዎችን ወደ ሀብትነት ለመቀየርና ምርትና ምርታማነት እንዲያድግ ወጥነት ባለው መልኩ የመደገፍ ስራ ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
በጉብኝቱ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራር አባላት፣ ሞዴል አርሶ አደሮችና ሌሎችም የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025