የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ከአሜሪካ ልዑክ ጋር ተወያየ

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፦ የዓለም የንግድ ድርጅት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ከአሜሪካ ልዑካን ቡድን ጋር ዛሬ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ውይይት አድርጓል።

የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ስብሰባ ነገ ይካሄዳል።

ለአባልነቱ የሚደራደረው የኢትዮጵያ ቡድን በ5ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ላይ ቡድን ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ዛሬ በሁለተኛ ቀን ውሎው ከአሜሪካ ልዑካን ቡድን ጋር ውይይት አድርጓል።

የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ቡድኑ ከአሜሪካ ልዑክ ጋር ያደረገው ውይይት በሁለትዮሽ የገበያ መዳረሻ ድርድር ዙሪያ ያተኮረ መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።


ወደ ፊት የገበያ ዕድሎችን ከማስፋት አንጻር በአገልግሎት፣ በግብርና እና ሌሎች ምርቶች የገበያ ዕድል ዙሪያ ከአሜሪካ በኩል ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ መሰጠቱን አመልክተዋል።

የሁለቱ ሀገራት የንግድ ግንኙነት መርህ ተኮር ሆኖ በሚጠናከርበት አግባብ ላይ የጋራ ግንዛቤ መፈጠሩንም ተናግረዋል።

የዓለም የንግድ ድርጅት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ትናንት ከአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጋር ውይይት ማድረጉ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025