
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፦ የዓለም የንግድ ድርጅት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ከአሜሪካ ልዑካን ቡድን ጋር ዛሬ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ውይይት አድርጓል።
የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ስብሰባ ነገ ይካሄዳል።
ለአባልነቱ የሚደራደረው የኢትዮጵያ ቡድን በ5ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ላይ ቡድን ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ዛሬ በሁለተኛ ቀን ውሎው ከአሜሪካ ልዑካን ቡድን ጋር ውይይት አድርጓል።
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ቡድኑ ከአሜሪካ ልዑክ ጋር ያደረገው ውይይት በሁለትዮሽ የገበያ መዳረሻ ድርድር ዙሪያ ያተኮረ መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

ወደ ፊት የገበያ ዕድሎችን ከማስፋት አንጻር በአገልግሎት፣ በግብርና እና ሌሎች ምርቶች የገበያ ዕድል ዙሪያ ከአሜሪካ በኩል ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ መሰጠቱን አመልክተዋል።
የሁለቱ ሀገራት የንግድ ግንኙነት መርህ ተኮር ሆኖ በሚጠናከርበት አግባብ ላይ የጋራ ግንዛቤ መፈጠሩንም ተናግረዋል።
የዓለም የንግድ ድርጅት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ትናንት ከአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጋር ውይይት ማድረጉ የሚታወስ ነው።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026