
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፦ የዓለም የንግድ ድርጅት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ከአሜሪካ ልዑካን ቡድን ጋር ዛሬ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ውይይት አድርጓል።
የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ስብሰባ ነገ ይካሄዳል።
ለአባልነቱ የሚደራደረው የኢትዮጵያ ቡድን በ5ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ላይ ቡድን ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ዛሬ በሁለተኛ ቀን ውሎው ከአሜሪካ ልዑካን ቡድን ጋር ውይይት አድርጓል።
የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ቡድኑ ከአሜሪካ ልዑክ ጋር ያደረገው ውይይት በሁለትዮሽ የገበያ መዳረሻ ድርድር ዙሪያ ያተኮረ መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

ወደ ፊት የገበያ ዕድሎችን ከማስፋት አንጻር በአገልግሎት፣ በግብርና እና ሌሎች ምርቶች የገበያ ዕድል ዙሪያ ከአሜሪካ በኩል ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ መሰጠቱን አመልክተዋል።
የሁለቱ ሀገራት የንግድ ግንኙነት መርህ ተኮር ሆኖ በሚጠናከርበት አግባብ ላይ የጋራ ግንዛቤ መፈጠሩንም ተናግረዋል።
የዓለም የንግድ ድርጅት የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን ትናንት ከአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጋር ውይይት ማድረጉ የሚታወስ ነው።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026