አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ)፦ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎታቸውን በማላቅ በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚረዳቸው መሆኑን ስልጠናውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ወጣቶች ገለጹ።
ስልጠናው ለሚሰሩት ስራ ተጨማሪ አቅምን እንደሚፈጠረላቸውም ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና ኤኒሼቲቭ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
ኤኒሼቲቩ "ትውልድ ይማር፣ ትውልድ ይሰልጥን፣ ከዓለም ጋር ይፎካከር" በሚል እሳቤ ወጣቶች የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን በማዳበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ብቁ ለማድረግ እየተተገበረ ይገኛል፡፡
ኤኒሼቲቩ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት እንዲጨብጡ የሚያስችል ነው።
ስልጠናውን ያጠናቀቁ ወጣቶች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተለዋዋጭ ሁኔታዎች ውስጥ ከሚፈጠሩ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር ራሳቸውን በፍጥነት እንዲያራምዱ የኮደርስ ስልጠናው ወሳኝ ነው፡፡
ከስራዋ ጎን ለጎን አራቱንም ስልጠናዎች በማጠናቀቅ ምስክር ወረቀት ያገኘችው ትዕግስት ጉዱ እንዳለችው ስልጠናው ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ ነው።
ስልጠናው ከፅሁፍ በተጨማሪ በምስል ተደግፎ መሰጠቱ ሳቢ እንደሚያደርገው የገለፀው ይድነቃቸው ተስፋዬ በበኩሉ በስልጠናው ያገኘው እውቀት ለሚሰራው ስራ ተጨማሪ አቅም መሆኑን ተናግሯል።
ስልጠናው በአለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያጎለብት በመሆኑ እድሉን በመጠቀም ራስን ከዘመኑ ጋር ማዘመን ያስፈልጋል ብለዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰለሞን አማረ በበኩላቸው በመዲናዋ በቀጣዮቹ ሶስት አመታት በአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ መርሃግብር 300ሺህ ነዋሪዎችን ለማብቃት ታቅዷል ብለዋል።
ስልጠናው ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017ዓ.ም ድረስ ከ165 ሺህ በላይ ወጣቶች ሥልጠናውን እየተከታተሉ ሲሆን 56 ሺህ ያህሉ ደግሞ ምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
ስልጠናው የዲጂታል ክህሎትን በማበልጸግ ስማርት ሲቲን ለመፍጠር የሚያግዝ በመሆኑ በከተማዋ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ ቢሮዎች ሰራተኞቻቸው ስልጠናውን እንዲከታተሉ ማበረታታት እንዳለባቸው አስረድተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025