የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኮደርስ ስልጠናው የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ክህሎትን ያሳደገ ነው

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ)፦ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎታቸውን በማላቅ በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚረዳቸው መሆኑን ስልጠናውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ወጣቶች ገለጹ።

ስልጠናው ለሚሰሩት ስራ ተጨማሪ አቅምን እንደሚፈጠረላቸውም ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም የአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና ኤኒሼቲቭ ማስጀመራቸው ይታወሳል።

ኤኒሼቲቩ "ትውልድ ይማር፣ ትውልድ ይሰልጥን፣ ከዓለም ጋር ይፎካከር" በሚል እሳቤ ወጣቶች የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን በማዳበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ብቁ ለማድረግ እየተተገበረ ይገኛል፡፡

ኤኒሼቲቩ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት እንዲጨብጡ የሚያስችል ነው።

ስልጠናውን ያጠናቀቁ ወጣቶች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተለዋዋጭ ሁኔታዎች ውስጥ ከሚፈጠሩ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር ራሳቸውን በፍጥነት እንዲያራምዱ የኮደርስ ስልጠናው ወሳኝ ነው፡፡

ከስራዋ ጎን ለጎን አራቱንም ስልጠናዎች በማጠናቀቅ ምስክር ወረቀት ያገኘችው ትዕግስት ጉዱ እንዳለችው ስልጠናው ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ ነው።

ስልጠናው ከፅሁፍ በተጨማሪ በምስል ተደግፎ መሰጠቱ ሳቢ እንደሚያደርገው የገለፀው ይድነቃቸው ተስፋዬ በበኩሉ በስልጠናው ያገኘው እውቀት ለሚሰራው ስራ ተጨማሪ አቅም መሆኑን ተናግሯል።

ስልጠናው በአለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያጎለብት በመሆኑ እድሉን በመጠቀም ራስን ከዘመኑ ጋር ማዘመን ያስፈልጋል ብለዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰለሞን አማረ በበኩላቸው በመዲናዋ በቀጣዮቹ ሶስት አመታት በአምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ መርሃግብር 300ሺህ ነዋሪዎችን ለማብቃት ታቅዷል ብለዋል።

ስልጠናው ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017ዓ.ም ድረስ ከ165 ሺህ በላይ ወጣቶች ሥልጠናውን እየተከታተሉ ሲሆን 56 ሺህ ያህሉ ደግሞ ምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

ስልጠናው የዲጂታል ክህሎትን በማበልጸግ ስማርት ሲቲን ለመፍጠር የሚያግዝ በመሆኑ በከተማዋ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ ቢሮዎች ሰራተኞቻቸው ስልጠናውን እንዲከታተሉ ማበረታታት እንዳለባቸው አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026