
ባህርዳር ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ጥራቱ የተጠበቀ ዘር ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ትኩረት መደረጉን የክልሉ የግብርና ጥራትና ደህንነት ባለስልጣን አስገነዘበ ።
አርሶ አደሩ የዘር ጥራት ማረጋገጫ የተለጠፈበትን ትክክለኛ ዘር ለይቶ ሊጠቀም እንደሚገባም ባለስልጣኑ አሳስቧል።
በባለስልጣኑ የዘር ጥራትና ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ጉርሜሳ እጀታ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት በክልሉ በባለፈው የምርት ዘመን በ12ሺህ 791 ሄክታር መሬት ላይ 18 አይነት የሰብል ዘር የማባዛት ስራ ተከናውኗል።
የዘር ብዜት ስራውም በመንግስት፣ በድርጅቶች፣ በዩኒየኖች፣ በምርምር ማዕከላት፣ በዩኒቨርስቲዎችና በግልለሰቦች ደረጃ መከናወኑን ገልጸዋል።
በማባዣዎች ከተመረተው ዘር ውስጥ 220ሺህ 371 ኩንታል ዘር ጥራቱን ጠብቆ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል ።
ከተሰበሰበው ውስጥም 190 ሺህ ኩንታል ዘር ተበጥሮ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
የተበጠረውን ዘር በላብራቶሪ በማረጋገጥ የጥራት ማረጋገጫ የተለጠፈበት መሆኑን ጠቁመው የበቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍና ሌሎች የሰብል አይነቶች ይገኙበታል ብለዋል።
አርሶ አደሩም በመጪው የመኽር ወቅት የዘር ጥራት ማረጋገጫ የተለጠፈበትን ትክክለኛ ዘር በመጠቀም የሰብል ምርታማነትን እንዲያሳድግ መልእክት አስተላልፈዋል።
ባለፈው ምርት ወቅት በበቆሎ ዘር ብቻ ተለጥፎ ይቀርብ የነበረው የጥራት ማረጋገጫ ዘንድሮ በሁሉም የሰብል አይነቶች በመለጠፍ የሚቀርብ መሆኑን አስታውቀዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026