
ባህርዳር ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ጥራቱ የተጠበቀ ዘር ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ትኩረት መደረጉን የክልሉ የግብርና ጥራትና ደህንነት ባለስልጣን አስገነዘበ ።
አርሶ አደሩ የዘር ጥራት ማረጋገጫ የተለጠፈበትን ትክክለኛ ዘር ለይቶ ሊጠቀም እንደሚገባም ባለስልጣኑ አሳስቧል።
በባለስልጣኑ የዘር ጥራትና ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ጉርሜሳ እጀታ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት በክልሉ በባለፈው የምርት ዘመን በ12ሺህ 791 ሄክታር መሬት ላይ 18 አይነት የሰብል ዘር የማባዛት ስራ ተከናውኗል።
የዘር ብዜት ስራውም በመንግስት፣ በድርጅቶች፣ በዩኒየኖች፣ በምርምር ማዕከላት፣ በዩኒቨርስቲዎችና በግልለሰቦች ደረጃ መከናወኑን ገልጸዋል።
በማባዣዎች ከተመረተው ዘር ውስጥ 220ሺህ 371 ኩንታል ዘር ጥራቱን ጠብቆ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል ።
ከተሰበሰበው ውስጥም 190 ሺህ ኩንታል ዘር ተበጥሮ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
የተበጠረውን ዘር በላብራቶሪ በማረጋገጥ የጥራት ማረጋገጫ የተለጠፈበት መሆኑን ጠቁመው የበቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍና ሌሎች የሰብል አይነቶች ይገኙበታል ብለዋል።
አርሶ አደሩም በመጪው የመኽር ወቅት የዘር ጥራት ማረጋገጫ የተለጠፈበትን ትክክለኛ ዘር በመጠቀም የሰብል ምርታማነትን እንዲያሳድግ መልእክት አስተላልፈዋል።
ባለፈው ምርት ወቅት በበቆሎ ዘር ብቻ ተለጥፎ ይቀርብ የነበረው የጥራት ማረጋገጫ ዘንድሮ በሁሉም የሰብል አይነቶች በመለጠፍ የሚቀርብ መሆኑን አስታውቀዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026