የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከአበዳሪዎች ጋር በተደረጉ ድርድሮች ኢትዮጵያ የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ አግኝታለች-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 11/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎች ጋር ባደረገችው የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።


የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፥ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ ኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ማሻሻያውን ተከትሎ ጤናማ የእዳ አስተዳደር እንዲኖር እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።


በዚህም ከአበዳሪዎች ጋር በተደረጉ ድርድሮች ኢትዮጵያ የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ ማግኘቷን አመልክተዋል።


ይህም ኢትዮጵያ ባለባት የእዳ ጫና ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ ተጽእኖ እንዳለው ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ አግባብነት የሌላቸው እዳዎች እንዲሰረዙ እና በአፍሪካ ላይ የተጫነው እዳ እንዲቃለል መስራቷን እንደምትቀጥል ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026