
አዲስ አበባ፤መጋቢት 11/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎች ጋር ባደረገችው የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፥ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ ኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ማሻሻያውን ተከትሎ ጤናማ የእዳ አስተዳደር እንዲኖር እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
በዚህም ከአበዳሪዎች ጋር በተደረጉ ድርድሮች ኢትዮጵያ የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ ማግኘቷን አመልክተዋል።
ይህም ኢትዮጵያ ባለባት የእዳ ጫና ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ ተጽእኖ እንዳለው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ አግባብነት የሌላቸው እዳዎች እንዲሰረዙ እና በአፍሪካ ላይ የተጫነው እዳ እንዲቃለል መስራቷን እንደምትቀጥል ገልጸዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026