
አዲስ አበባ፤መጋቢት 11/2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎች ጋር ባደረገችው የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፥ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ ኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ማሻሻያውን ተከትሎ ጤናማ የእዳ አስተዳደር እንዲኖር እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
በዚህም ከአበዳሪዎች ጋር በተደረጉ ድርድሮች ኢትዮጵያ የ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ ማግኘቷን አመልክተዋል።
ይህም ኢትዮጵያ ባለባት የእዳ ጫና ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ ተጽእኖ እንዳለው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ አግባብነት የሌላቸው እዳዎች እንዲሰረዙ እና በአፍሪካ ላይ የተጫነው እዳ እንዲቃለል መስራቷን እንደምትቀጥል ገልጸዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026