የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ እስከ አንድ ሚሊዮን ለሚጠጉ ዜጎች በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መስጠት የሚያስችል አቅም አለ - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፍቃዱ

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስከ አንድ ሚሊዮን ለሚጠጉ ዜጎች በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መስጠት የሚያስችል አቅም አለ ሲሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፍቃዱ ገልጸዋል።

በክልሉ በ5ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የላቀ አፈጻጸም ማስመዝገብ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በዲጂታል ክህሎት የበለጸገ ማህበረሰብ መፍጠር በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን ያስችላል ብለዋል።


በኢኮኖሚና በስልጣኔ ተወዳዳሪ ለመሆን ብቃት ያለው እና የሰለጠነ ዜጋ መፍጠር ተገቢ መሆንም ገልጸዋል።

በክልሉ በዘርፉ የወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚነት ለማሳደግ ስልጠናው ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለውም ጠቁመዋል።

በክልሉ እስከ አንድ ሚሊዮን ለሚጠጉ ዜጎች ስልጠና መስጠት የሚያስችል አቅም እንዳለ ገልጸው

ወጣቶች በነጻ የተገኘውን እድል መጠቀም እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ዜጎች በአለም አቀፍ ደረጃ ተግባቦት መፍጠር እንዲችሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት ሊኖራቸው ይገባል ያሉት ኃላፊው ለዚህም የሁሉንም አካላት የተቀናጀ ጥረት ማድረግ እንዳለባቸውም አመላክተዋል።


በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ አመንጪነት የተገኘው የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ኢትዮጵያ የጀመረችውን የልማት እና የእድገት ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለውም አብራርተዋል።

መንግስት ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቀውን ስልጠና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያመቻቸውን ነጻ እድል መጠቀም እንደሚገባም አቶ አንተነህ ጥሪ አቅርበዋል።

በክልሉ በየደረጃው ያለው አመራር እና ባለሙያ በስልጠናው መሳተፍ እንዳለበት ጠቁመው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችም በነጻ የተገኘውን እድል መጠቀም እንዳለባቸው ገልጸዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ በበኩላቸው እንደ ክልል በኢትዮ ኮደርስ የስልጠና እድል ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ስልጠናውን በሚፈለገው መጠን እና ጊዜ መስጠት እንዲቻል ከርዕሰ መስተዳድሩ ጀምሮ አጠቃላይ አመራሩ የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


ከዲጂታል ቴክኖሎጂው ጋር የተላመደ ማህበረሰብ ለመፍጠር የስልጠናው አስፈላጊነት የጎላ መሆኑን መግለጻቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

ህብረተሰቡ በጊዜና በቦታ ሳይገደብ ስልጠናውን መከታተል የሚችልበት ስርዓት መዘርጋቱን የተናገሩት ኃላፊው ኢትዮ ቴሌኮም ስልጠናው ስኬታማ እንዲሆን ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት በማቅረቡ አመስግነዋል።

የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ በበኩላቸው በክልሉ ለዜጎች የሚሰጠው ስልጠና ውጤታማ እንዲሆን የሁሉንም አካላት የጋራ ጥረት ይጠይቃል ነው ያሉት።

በአፈጻጸም በኩል የተስተዋሉ መልካም ልምዶችን ማስቀጠል እና ውስንነቶችን በማረም ስልጠናው የዜጎችን ህይወት መቀየር እንዲችል በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026