የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ስማርት ሲቲ ግንባታን ለማሳለጥ የተቋማትን አሰራር ቴክኖሎጂ መር እየተደረገ ነው

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 20/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማን የስማርት ሲቲ ጉዞ ለማሳለጥ የተቋማትን አሰራር ቴክኖሎጂ መር የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማዋ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ቱሉ ጥላሁን (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ የስምንት አመት ስትራቴጂክ ፕላን ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን አንስተዋል።

ስትራቴጂ ፕላኑ መተግበር ከጀመረ ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑን ጠቅሰው፣በዚህ ጊዜ ውስጥ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል።


ከእነዚህ ውስጥ የተቋማትን አሰራር በቴክኖሎጂ ማሳለጥ የሚያስችል የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግንባታ አንዱ ነው ብለዋል።

በአሁን ጊዜ ተቋማት በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲገነቡና እንዲጠቀሙ በመደረጉ አገልግሎት አሰጣጡን ማቀላጠፍ የተቻለ መሆኑንም አመልክተዋል።

ለአብነትም በመሬት አስተዳደር፣ በሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት የመሳሰሉ ቁልፍ ተቋማትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለመደገፍ የተጀመረው አሰራር ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል።

እንደ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ገለጻ፣በከተማዋ የተከናወኑ የኮሪደር ልማቶች የስማርት ሲቲ ግንባታው ወሳኝ ሚና አላቸው።

የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከተማዋ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅናና ተቀባይነት እንዲጨምር ማድረጉንም ነው የተናገሩት።

በአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር አእምሮ ካሳ በበኩላቸው፣ ቀደም ሲል የነበረው የተቋሙ አሰራር ቴክኖሎጂ ባለመደራጀቱ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ተደጋጋሚ ቅሬታ ይነሳ እንደነበር አስታውሰዋል።


ተቋሙ ከ2016 ጀምሮ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መገንባቱን ተከትሎ የሚሰጣቸውን አገልግሎት ከወረቀት ውጭ በማድረግ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ነው ያሉት።

ከዚህም በተጨማሪ ቴክኖሎጂውን ከሌሎች ተቋማት ጋር በማስተሳሰር የአገልግሎት አሰጣጡን በማቀላጠፍ የነዋሪውን እንግልት በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የአገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ ለማቀላጠፍ ከሌሎች ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂ የተሳሰረ ግንኙነት መፈጠሩንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026