የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ስማርት ሲቲ ግንባታን ለማሳለጥ የተቋማትን አሰራር ቴክኖሎጂ መር እየተደረገ ነው

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 20/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማን የስማርት ሲቲ ጉዞ ለማሳለጥ የተቋማትን አሰራር ቴክኖሎጂ መር የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የከተማዋ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ቱሉ ጥላሁን (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ የስምንት አመት ስትራቴጂክ ፕላን ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን አንስተዋል።

ስትራቴጂ ፕላኑ መተግበር ከጀመረ ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑን ጠቅሰው፣በዚህ ጊዜ ውስጥ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል።


ከእነዚህ ውስጥ የተቋማትን አሰራር በቴክኖሎጂ ማሳለጥ የሚያስችል የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግንባታ አንዱ ነው ብለዋል።

በአሁን ጊዜ ተቋማት በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲገነቡና እንዲጠቀሙ በመደረጉ አገልግሎት አሰጣጡን ማቀላጠፍ የተቻለ መሆኑንም አመልክተዋል።

ለአብነትም በመሬት አስተዳደር፣ በሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት የመሳሰሉ ቁልፍ ተቋማትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለመደገፍ የተጀመረው አሰራር ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል።

እንደ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ገለጻ፣በከተማዋ የተከናወኑ የኮሪደር ልማቶች የስማርት ሲቲ ግንባታው ወሳኝ ሚና አላቸው።

የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ በከተማዋ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከተማዋ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅናና ተቀባይነት እንዲጨምር ማድረጉንም ነው የተናገሩት።

በአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር አእምሮ ካሳ በበኩላቸው፣ ቀደም ሲል የነበረው የተቋሙ አሰራር ቴክኖሎጂ ባለመደራጀቱ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ተደጋጋሚ ቅሬታ ይነሳ እንደነበር አስታውሰዋል።


ተቋሙ ከ2016 ጀምሮ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መገንባቱን ተከትሎ የሚሰጣቸውን አገልግሎት ከወረቀት ውጭ በማድረግ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ነው ያሉት።

ከዚህም በተጨማሪ ቴክኖሎጂውን ከሌሎች ተቋማት ጋር በማስተሳሰር የአገልግሎት አሰጣጡን በማቀላጠፍ የነዋሪውን እንግልት በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የአገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ ለማቀላጠፍ ከሌሎች ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂ የተሳሰረ ግንኙነት መፈጠሩንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026