
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከተባበበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላትን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር እንደምትሻ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ ላይ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ ሽግግር እንዲሁም በሌሎች መስኮች ላይ ያላትን ዓለም አቀፍ ትብብርን የማሳደግ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።
በዚህ ረገድም ኢኖንፎርሜሽ እና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በዲጂታል ቴክኖሎጂ በፈጠራቸው ማዕቀፎች ያላትን ተጠቃሚነት ለማጎልበት እንደምትሰራ አመልክተዋል።
ከተመድ የቴክኖሎጂ የስራ ክፍሎች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ይሰራል ነው ያሉት።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በመሰረተ ልማት፣ በአስተዳደርና በሰው አቅም ግንባታ ላይ በማተኮር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዕድገት የሚያጎለብቱ ጠንካራ ፖሊሲዎች እና ተቋማት ማቋቋሟን በውይይቱ ወቅት አንስተዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) የደቡባዊ ንፍቀ ክበብ ሃገራት በዲጂታል ዓለም እኩል ተጠቃሚ እና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ የአሰራር ማዕቀፎች ላይ ማሻሻያ ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል።
ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት የተመድን የዲጂታል ዘርፍ እድሎችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ማቅረባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026