
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከተባበበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላትን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር እንደምትሻ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ ላይ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ ሽግግር እንዲሁም በሌሎች መስኮች ላይ ያላትን ዓለም አቀፍ ትብብርን የማሳደግ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።
በዚህ ረገድም ኢኖንፎርሜሽ እና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በዲጂታል ቴክኖሎጂ በፈጠራቸው ማዕቀፎች ያላትን ተጠቃሚነት ለማጎልበት እንደምትሰራ አመልክተዋል።
ከተመድ የቴክኖሎጂ የስራ ክፍሎች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ይሰራል ነው ያሉት።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ በመሰረተ ልማት፣ በአስተዳደርና በሰው አቅም ግንባታ ላይ በማተኮር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዕድገት የሚያጎለብቱ ጠንካራ ፖሊሲዎች እና ተቋማት ማቋቋሟን በውይይቱ ወቅት አንስተዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) የደቡባዊ ንፍቀ ክበብ ሃገራት በዲጂታል ዓለም እኩል ተጠቃሚ እና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ የአሰራር ማዕቀፎች ላይ ማሻሻያ ማድረግ እንደሚገባ አመልክተዋል።
ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት የተመድን የዲጂታል ዘርፍ እድሎችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ማቅረባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026