የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የጥራት መንደር በዓመት ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን በላይ የገቢና ወጪ ምርቶችን ጥራት የማረጋገጥ አቅም ፈጥሯል - ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- የለውጡ ትሩፋት የሆነው የጥራት መንደር በዓመት ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን በላይ የገቢና ወጪ ንግድ ምርቶችን ጥራት የማረጋገጥ አስተማማኝ አቅም መፍጠሩን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ባለፉት ሰባት ዓመታት የንግድና የምርት ጥራት ፍተሻ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸውን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ንግድ ተወዳዳሪ መሆን የሚያስችላትን የጥራት መንደር ባለፈው ህዳር ወር 2017 ዓ.ም መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የጥራት መንደር ለዘላቂ ዕድገት መሰረት የሚጥልና የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጅማሮ የሚያበስር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የጥራት መንደር የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ስነ-ልክ ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት እና የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣንን የያዘ ነው፡፡

ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የጥራት ቁጥጥር የማድረግ አቅም በእጅጉ ተሻሽሏል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ንግድ ዘርፉን ዕድገትና ተወዳዳሪነት ለማሻሻል፥ በአፍሪካ ግዙፉን የጥራት መንደር መገንባቷን አንስተዋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አመራር ሰጪነትና በጋራ ጥረት እውን የሆነው የጥራት መንደር ዓለም ከደረሰበት ደረጃ ጋር የሚሄዱ ዘመናዊ የፍተሻ ላቦራቶሪዎች የተገጠሙለት መሆኑን ገልጸዋል።

መንግስት ኢትዮጵያን በወጪ ንግድ በአፍሪካ ቀዳሚ ለማድረግ የያዘውን ራዕይ ለማሳካትም፥ የለውጡ ትሩፋት የሆነው የጥራት መንደር ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡

ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ጥራት ማረጋገጫና የፍተሻ መሰረተ ልማት፥ የበለጸገች ኢትዮጵያ እውን የማድረግ ጉዞን ለማሳካት የሚያስችል መሆኑንም አስረድተዋል፡፡


የጥራት መንደር በዓመት ከ3 ነጥብ 8 ሚሊዮን ቶን በላይ ገቢ እና ለ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቶን የወጪ ንግድ ምርቶች ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ፍተሻ የማድረግ አስተማማኝ አቅም መፍጠሩንም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ካሏት የጥራት ደረጃዎች 80 በመቶ ያህሉ ከዓለም አቀፉ ደረጃዎች ጋር የተጣጣሙ ናቸው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ይህም ሀገሪቱ በዓለም የንግድ መስተጋብር የተሻለ ተሳትፎ እንዲኖራት ያስችላል ብለዋል፡፡

የጥራት መንደር ኢትዮጵያ በጥራት ፍተሻ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጎልታ የምትታይበትን እድል የፈጠረ መሆኑንም ገለጸዋል፡፡

ዘመናዊ የፍተሻ መሣሪያዎችን በማሟላት የተሻሻለ አቅም የፈጠረው የጥራት መንደር ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ ደረጃዎች ጋር ተስማሚ ጥራት እንድታረጋግጥ፣ የቴክኒክ መሰናክሎችን እንድትቀንስና በዓለም አቀፍ ንግድ ያላትን ተሳትፎ እንድታሻሽል ጉልህ አስተዋፅኦ አለው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026