
አዲስ አበባ፤መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሰባት አመታት በለውጡ አመታት የተገኙ ስኬቶችን ለማስፋት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ።
የሰባት አመታት የለውጥ ጉዞና የተገኙ ውጤቶችን የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ በኦሮሞ ባህል ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአውደ ርዕዩን የጎበኙ አካላት በለውጡ ዓመታት በበርካታ ዘፎች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፥ እነዚህ ውጤቶች የበለጠ እንዲጠናከሩ በቴክኖሎጂ ማስደገፍ ይገባል ብለዋል።
አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል አቶ አብዲሳ ታደሰ፥ በለውጡ አመታት በክልሉ በተለያዩ ተቋማት የቀረቡ የልማት ውጤቶች ወደ እድገትና ከፍታ እየተራመድን መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
እነዚህን የልማት ውጤቶች በቴክኖሎጂ በመደገፍ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድ ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።
አቶ ዮናታን ጫሊ በበኩላቸው፥ በለውጡ አመታት በሁሉም መስኮች የተሰሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አንስተው፥የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
እነዚህ የልማት ውጤቶች የተገኙት በብዙ ውጣ ውረድ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከዚህ ልምድ በመውሰድ ስራዎች በቴክኖሎጂ የተደገፉ እንዲሆኑ መትጋት ይገባልም ብለዋል።
ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ደረጀ ጥላዬ በበኩላቸው፥ በክልሉ በተለይም በግብርና፤ በትምህርትና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ተስፋ ሰጪ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።
በግንባታ ዘርፍ ላይ በቴክኖሎጂ የመጡት ለውጦች አበረታች መሆናቸውን ገልፀው ይበልጥ ለማስቀጠል በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን መዘርጋትና ማስፋት ይገባል ሲሉ ገልጸዋል።
ባለፉት ሰባት አመታት የኦሮሞን ባህልና ትውፊት የሚገልጹ የተለያዩ ቅርሶች ካሉበት ተሰብስበው ለቱሪዝም አገልግሎት እንዲውሉ መደረጉን የተናገሩት ደግሞ በኦሮሞ ባህል ማዕከል የሙዚየም ልማትና የተንቀሳቃሽ ቅርስ ቡድን መሪ ወይዘሮ ቅድስት ለገሰ ናቸው።
ለወደፊቱም ያሉንን ሀብቶች በቴክኖሎጂ በማዳበርና በማስተዋወቅ ገቢ እንዲያመጣ እንሰራለን ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026