
አዲስ አበባ፤መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሰባት አመታት በለውጡ አመታት የተገኙ ስኬቶችን ለማስፋት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ።
የሰባት አመታት የለውጥ ጉዞና የተገኙ ውጤቶችን የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ በኦሮሞ ባህል ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአውደ ርዕዩን የጎበኙ አካላት በለውጡ ዓመታት በበርካታ ዘፎች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፥ እነዚህ ውጤቶች የበለጠ እንዲጠናከሩ በቴክኖሎጂ ማስደገፍ ይገባል ብለዋል።
አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል አቶ አብዲሳ ታደሰ፥ በለውጡ አመታት በክልሉ በተለያዩ ተቋማት የቀረቡ የልማት ውጤቶች ወደ እድገትና ከፍታ እየተራመድን መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
እነዚህን የልማት ውጤቶች በቴክኖሎጂ በመደገፍ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድ ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።
አቶ ዮናታን ጫሊ በበኩላቸው፥ በለውጡ አመታት በሁሉም መስኮች የተሰሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አንስተው፥የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
እነዚህ የልማት ውጤቶች የተገኙት በብዙ ውጣ ውረድ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከዚህ ልምድ በመውሰድ ስራዎች በቴክኖሎጂ የተደገፉ እንዲሆኑ መትጋት ይገባልም ብለዋል።
ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ደረጀ ጥላዬ በበኩላቸው፥ በክልሉ በተለይም በግብርና፤ በትምህርትና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ተስፋ ሰጪ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።
በግንባታ ዘርፍ ላይ በቴክኖሎጂ የመጡት ለውጦች አበረታች መሆናቸውን ገልፀው ይበልጥ ለማስቀጠል በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን መዘርጋትና ማስፋት ይገባል ሲሉ ገልጸዋል።
ባለፉት ሰባት አመታት የኦሮሞን ባህልና ትውፊት የሚገልጹ የተለያዩ ቅርሶች ካሉበት ተሰብስበው ለቱሪዝም አገልግሎት እንዲውሉ መደረጉን የተናገሩት ደግሞ በኦሮሞ ባህል ማዕከል የሙዚየም ልማትና የተንቀሳቃሽ ቅርስ ቡድን መሪ ወይዘሮ ቅድስት ለገሰ ናቸው።
ለወደፊቱም ያሉንን ሀብቶች በቴክኖሎጂ በማዳበርና በማስተዋወቅ ገቢ እንዲያመጣ እንሰራለን ብለዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026