የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በለውጡ አመታት የተገኙ ስኬቶችን ለማስፋት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ማጠናከር ይገባል

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሰባት አመታት በለውጡ አመታት የተገኙ ስኬቶችን ለማስፋት በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ማጠናከር እንደሚገባ ተመለከተ።

የሰባት አመታት የለውጥ ጉዞና የተገኙ ውጤቶችን የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ በኦሮሞ ባህል ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የአውደ ርዕዩን የጎበኙ አካላት በለውጡ ዓመታት በበርካታ ዘፎች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፥ እነዚህ ውጤቶች የበለጠ እንዲጠናከሩ በቴክኖሎጂ ማስደገፍ ይገባል ብለዋል።

አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል አቶ አብዲሳ ታደሰ፥ በለውጡ አመታት በክልሉ በተለያዩ ተቋማት የቀረቡ የልማት ውጤቶች ወደ እድገትና ከፍታ እየተራመድን መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

እነዚህን የልማት ውጤቶች በቴክኖሎጂ በመደገፍ የህዝቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ ጠቅሰው በዚህ ረገድ ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

አቶ ዮናታን ጫሊ በበኩላቸው፥ በለውጡ አመታት በሁሉም መስኮች የተሰሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አንስተው፥የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሱ መሆናቸውን ተናግረዋል።

እነዚህ የልማት ውጤቶች የተገኙት በብዙ ውጣ ውረድ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከዚህ ልምድ በመውሰድ ስራዎች በቴክኖሎጂ የተደገፉ እንዲሆኑ መትጋት ይገባልም ብለዋል።

ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ ደረጀ ጥላዬ በበኩላቸው፥ በክልሉ በተለይም በግብርና፤ በትምህርትና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ተስፋ ሰጪ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

በግንባታ ዘርፍ ላይ በቴክኖሎጂ የመጡት ለውጦች አበረታች መሆናቸውን ገልፀው ይበልጥ ለማስቀጠል በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን መዘርጋትና ማስፋት ይገባል ሲሉ ገልጸዋል።

ባለፉት ሰባት አመታት የኦሮሞን ባህልና ትውፊት የሚገልጹ የተለያዩ ቅርሶች ካሉበት ተሰብስበው ለቱሪዝም አገልግሎት እንዲውሉ መደረጉን የተናገሩት ደግሞ በኦሮሞ ባህል ማዕከል የሙዚየም ልማትና የተንቀሳቃሽ ቅርስ ቡድን መሪ ወይዘሮ ቅድስት ለገሰ ናቸው።

ለወደፊቱም ያሉንን ሀብቶች በቴክኖሎጂ በማዳበርና በማስተዋወቅ ገቢ እንዲያመጣ እንሰራለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026