የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል የድርሻችንን እየተወጣን እንገኛለን - ዋና ኦዲተሮች

Apr 7, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን የክልሎችና የከተሞች ዋና ኦዲተሮች ገለፁ።

በድሬዳዋ የተካሄደው 10ኛው የክልሎች፣ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶች የምክክርና የልምድ ልውውጥ መድረክ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት ተጠናቋል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው ዋና ኦዲተሮች የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።

በድሬዳዋ ለሁለት ቀናት የተደረገው የልምድ ልውውጥና ምክክርም የኦዲት ስራ ጥራትን ለማረጋገጥ አቅም የፈጠሩበት እንደሆነም ተናግረዋል።


ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የሐረሪ ክልል ዋና ኦዲተር አቶ አብዱማሊክ በከር እንዳሉት፤ በክልሉ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ጥብቅ የኦዲት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ ቢሻው በበኩላቸው የምክክር መድረኩ ወጥ የሆነ የኦዲት ስራን ለመተግበር መደላድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

ከምክክር መድረኩ በኦዲት ስራዎች ላይ የገጠሙ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ልምዶች በመቅሰማቸው በቀጣይ የተሻለ የኦዲት ስራዎችን ለማከናወን የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚያግዛቸው ጠቁመዋል።


ከድሬዳዋ የቀሰሙትን ልምድ በመቀመርና በመተግበር ፈጣንና ቀልጣፋ የኦዲት አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አቅም እንደሚሆናቸው የገለፁት ደግሞ የሲዳማ ክልል ዋና ኦዲተር አቶ ሲምቦ ሽንብሩ ናቸው።

ባገኙት ተሞክሮም በቀጣይ የህዝብና የመንግስት በጀት በትክክል ስራ ላይ እንዲውል ጥራት ያለውና አመኔታ ያተረፈ የኦዲት አገልግሎትን ለውሳኔ ሰጪ አካላት ለማቅረብ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።


የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ዋና ኦዲተር አቶ ንጉሱ ገብረ ጊዮርጊስ በበኩላቸው በክልሉ በትላልቅ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተገቢውን የኦዲት ስራ ማከናወናቸውን ተናግረዋል።

የምክክር መድረኩ የኦዲት አገልግሎቱን ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላችውም ገልጸዋል።


የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ዋና ኦዲተሮችና ዳይሬክተሮች ከምክክር በኃላ በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ መሠረተ ልማቶችንና የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026