ድሬዳዋ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን የክልሎችና የከተሞች ዋና ኦዲተሮች ገለፁ።
በድሬዳዋ የተካሄደው 10ኛው የክልሎች፣ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶች የምክክርና የልምድ ልውውጥ መድረክ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት ተጠናቋል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው ዋና ኦዲተሮች የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።
በድሬዳዋ ለሁለት ቀናት የተደረገው የልምድ ልውውጥና ምክክርም የኦዲት ስራ ጥራትን ለማረጋገጥ አቅም የፈጠሩበት እንደሆነም ተናግረዋል።
ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የሐረሪ ክልል ዋና ኦዲተር አቶ አብዱማሊክ በከር እንዳሉት፤ በክልሉ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ጥብቅ የኦዲት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ ቢሻው በበኩላቸው የምክክር መድረኩ ወጥ የሆነ የኦዲት ስራን ለመተግበር መደላድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
ከምክክር መድረኩ በኦዲት ስራዎች ላይ የገጠሙ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ልምዶች በመቅሰማቸው በቀጣይ የተሻለ የኦዲት ስራዎችን ለማከናወን የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚያግዛቸው ጠቁመዋል።
ከድሬዳዋ የቀሰሙትን ልምድ በመቀመርና በመተግበር ፈጣንና ቀልጣፋ የኦዲት አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አቅም እንደሚሆናቸው የገለፁት ደግሞ የሲዳማ ክልል ዋና ኦዲተር አቶ ሲምቦ ሽንብሩ ናቸው።
ባገኙት ተሞክሮም በቀጣይ የህዝብና የመንግስት በጀት በትክክል ስራ ላይ እንዲውል ጥራት ያለውና አመኔታ ያተረፈ የኦዲት አገልግሎትን ለውሳኔ ሰጪ አካላት ለማቅረብ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ዋና ኦዲተር አቶ ንጉሱ ገብረ ጊዮርጊስ በበኩላቸው በክልሉ በትላልቅ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተገቢውን የኦዲት ስራ ማከናወናቸውን ተናግረዋል።
የምክክር መድረኩ የኦዲት አገልግሎቱን ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላችውም ገልጸዋል።
የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ዋና ኦዲተሮችና ዳይሬክተሮች ከምክክር በኃላ በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ መሠረተ ልማቶችንና የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025