
ድሬዳዋ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን የክልሎችና የከተሞች ዋና ኦዲተሮች ገለፁ።
በድሬዳዋ የተካሄደው 10ኛው የክልሎች፣ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶች የምክክርና የልምድ ልውውጥ መድረክ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት ተጠናቋል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው ዋና ኦዲተሮች የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።
በድሬዳዋ ለሁለት ቀናት የተደረገው የልምድ ልውውጥና ምክክርም የኦዲት ስራ ጥራትን ለማረጋገጥ አቅም የፈጠሩበት እንደሆነም ተናግረዋል።

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የሐረሪ ክልል ዋና ኦዲተር አቶ አብዱማሊክ በከር እንዳሉት፤ በክልሉ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ጥብቅ የኦዲት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ ቢሻው በበኩላቸው የምክክር መድረኩ ወጥ የሆነ የኦዲት ስራን ለመተግበር መደላድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
ከምክክር መድረኩ በኦዲት ስራዎች ላይ የገጠሙ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ልምዶች በመቅሰማቸው በቀጣይ የተሻለ የኦዲት ስራዎችን ለማከናወን የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚያግዛቸው ጠቁመዋል።

ከድሬዳዋ የቀሰሙትን ልምድ በመቀመርና በመተግበር ፈጣንና ቀልጣፋ የኦዲት አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አቅም እንደሚሆናቸው የገለፁት ደግሞ የሲዳማ ክልል ዋና ኦዲተር አቶ ሲምቦ ሽንብሩ ናቸው።
ባገኙት ተሞክሮም በቀጣይ የህዝብና የመንግስት በጀት በትክክል ስራ ላይ እንዲውል ጥራት ያለውና አመኔታ ያተረፈ የኦዲት አገልግሎትን ለውሳኔ ሰጪ አካላት ለማቅረብ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ዋና ኦዲተር አቶ ንጉሱ ገብረ ጊዮርጊስ በበኩላቸው በክልሉ በትላልቅ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተገቢውን የኦዲት ስራ ማከናወናቸውን ተናግረዋል።
የምክክር መድረኩ የኦዲት አገልግሎቱን ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላችውም ገልጸዋል።

የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ዋና ኦዲተሮችና ዳይሬክተሮች ከምክክር በኃላ በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ መሠረተ ልማቶችንና የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026