
ድሬዳዋ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን የክልሎችና የከተሞች ዋና ኦዲተሮች ገለፁ።
በድሬዳዋ የተካሄደው 10ኛው የክልሎች፣ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤቶች የምክክርና የልምድ ልውውጥ መድረክ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት ተጠናቋል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው ዋና ኦዲተሮች የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን ገልጸዋል።
በድሬዳዋ ለሁለት ቀናት የተደረገው የልምድ ልውውጥና ምክክርም የኦዲት ስራ ጥራትን ለማረጋገጥ አቅም የፈጠሩበት እንደሆነም ተናግረዋል።

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የሐረሪ ክልል ዋና ኦዲተር አቶ አብዱማሊክ በከር እንዳሉት፤ በክልሉ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ለታለመለት አላማ እንዲውል ጥብቅ የኦዲት ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር አቶ አመንቴ ቢሻው በበኩላቸው የምክክር መድረኩ ወጥ የሆነ የኦዲት ስራን ለመተግበር መደላድል የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
ከምክክር መድረኩ በኦዲት ስራዎች ላይ የገጠሙ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ልምዶች በመቅሰማቸው በቀጣይ የተሻለ የኦዲት ስራዎችን ለማከናወን የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚያግዛቸው ጠቁመዋል።

ከድሬዳዋ የቀሰሙትን ልምድ በመቀመርና በመተግበር ፈጣንና ቀልጣፋ የኦዲት አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አቅም እንደሚሆናቸው የገለፁት ደግሞ የሲዳማ ክልል ዋና ኦዲተር አቶ ሲምቦ ሽንብሩ ናቸው።
ባገኙት ተሞክሮም በቀጣይ የህዝብና የመንግስት በጀት በትክክል ስራ ላይ እንዲውል ጥራት ያለውና አመኔታ ያተረፈ የኦዲት አገልግሎትን ለውሳኔ ሰጪ አካላት ለማቅረብ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ዋና ኦዲተር አቶ ንጉሱ ገብረ ጊዮርጊስ በበኩላቸው በክልሉ በትላልቅ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተገቢውን የኦዲት ስራ ማከናወናቸውን ተናግረዋል።
የምክክር መድረኩ የኦዲት አገልግሎቱን ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላችውም ገልጸዋል።

የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ዋና ኦዲተሮችና ዳይሬክተሮች ከምክክር በኃላ በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ መሠረተ ልማቶችንና የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026