
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬትና መዋቅራዊ ሽግግር የበኩሉን ሚና እንዲወጣ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
በሹዋሊድ ክብረ በዓል ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ የፌዴራልና ክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ከርዕሰ መስተዳድሩ ጋር በመሆን በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱም በክልሉ ያለው የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴ፤ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የድንገተኛ አደጋ ማዕከልና የሲሲ ቲቪ የመንገድ ላይ የደህንነት ካሜራ ፕሮጀክትን ተመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ማስ ኢንጅነሪንግ ድርጅትን በጎበኙበት ወቅት እንደገለፁት በክልሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬትና መዋቅራዊ ሽግግር የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ለማስቻል እየተሰራ ነው።
በተለይም ከለውጡ ወዲህ የአምራች ዘርፉን ችግሮች በመለየት በተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች የተሻለ መነቃቃት መፈጠሩን ገልፀዋል።

ይህም ከለውጡ በፊት በነበረው የፖለቲካ መጠፋፋት የተፈናቃዮች መጠለያ የነበሩ ሼዶች አሁን ላይ የምርት ማዕከል በመሆን የአገርን ልማት ሊደግፉ የሚችሉ ስራዎች እየተሰራባቸው መሆኑን ገልፀዋል።
ለዘርፉ በተሰጠው ትኩረት በኢንዱስትሪ ዞኑ የሚመረቱ የመንገድ ዳር መብራቶች የሐረር ከተማ ኮሪደሮችን ከማድመቅ ባሻገር ለጥገና ምቹ እና ተመራጭ መሆናቸወንም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።
በከተማው ገቢራዊ እየሆኑ የሚገኙ የመንገድ ላይ የደህንነት ካሜራዎችና የድንገተኛ አደጋ ማዕከል ከከተማው ዕድገት ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎች እና ወንጀሎችን ቀድሞ ለመከላከል ያስችላሉ ብለዋል።
በተለይ ከእሳት አደጋ ጋር ተያይዞ ከማህበረሰቡ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውንም ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገልፀዋል።
በጉብኝቱ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልል ቅርንጫፍ ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ፤ የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም፤ የሐረሪ ጉባኤ አፈ-ጉባኤ አቶ ሙህየዲን አህመድ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመር፤የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች መገኘታቸውን የክልል ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026