
ደሴ፤መጋቢት 28/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በመኽር ወቅት ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም በማልማት የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው የ2017/2018 ምርት ዘመን የመኸር ሰብል ልማት እቅድን ለማሳካት በግብርና ፓኬጅ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስልጠናና የእቅድ ትውውቅ ማጠቃለያ መድረክ በደሴ ከተማ አካሂዷል።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቃልኪዳን ሽፈራው በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፥ በክልሉ የተሻሻሉ አሰራሮችን በመጠቀም የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።
በዚህም በመኽር ወቅቱ ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታገጠም በማልማት 115 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም በምርት ወቅቱ አጠቃላይ 5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን ከ187 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ የተያዘውን ግብ ለማሳካት አጋዥ እንደሚሆን አስረድተዋል።
ከኩታ ገጠም አስተራረስ ባሻገር አሲዳማ መሬት በኖራ በማከም፣ግብዓት በማቅረብ፣መካናይዜሽንን በማስፋፋትና ሌሎችም ተግባራት በማከናወን የታቀደውን ምርት ለማግኘት ከወዲሁ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም በምግብ ራስን ለመቻል፣ለኢንዱስትሪ ጥሬ እቃና ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማምረት ግብርናው የሌሎች ኢኮኖሚ ዘርፎች መሰረት መሆኑን ለማረጋገጥ አላማ ያደረገ ነው ሲሉ አስታውቀዋል።
በመድረኩ የክልል፣የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራር አካላት፣ የግብርና ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026