
ደሴ፤መጋቢት 28/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በመኽር ወቅት ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም በማልማት የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው የ2017/2018 ምርት ዘመን የመኸር ሰብል ልማት እቅድን ለማሳካት በግብርና ፓኬጅ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስልጠናና የእቅድ ትውውቅ ማጠቃለያ መድረክ በደሴ ከተማ አካሂዷል።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቃልኪዳን ሽፈራው በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፥ በክልሉ የተሻሻሉ አሰራሮችን በመጠቀም የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።
በዚህም በመኽር ወቅቱ ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታገጠም በማልማት 115 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም በምርት ወቅቱ አጠቃላይ 5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን ከ187 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ የተያዘውን ግብ ለማሳካት አጋዥ እንደሚሆን አስረድተዋል።
ከኩታ ገጠም አስተራረስ ባሻገር አሲዳማ መሬት በኖራ በማከም፣ግብዓት በማቅረብ፣መካናይዜሽንን በማስፋፋትና ሌሎችም ተግባራት በማከናወን የታቀደውን ምርት ለማግኘት ከወዲሁ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም በምግብ ራስን ለመቻል፣ለኢንዱስትሪ ጥሬ እቃና ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማምረት ግብርናው የሌሎች ኢኮኖሚ ዘርፎች መሰረት መሆኑን ለማረጋገጥ አላማ ያደረገ ነው ሲሉ አስታውቀዋል።
በመድረኩ የክልል፣የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራር አካላት፣ የግብርና ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026