
ደሴ፤መጋቢት 28/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በመኽር ወቅት ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም በማልማት የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው የ2017/2018 ምርት ዘመን የመኸር ሰብል ልማት እቅድን ለማሳካት በግብርና ፓኬጅ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስልጠናና የእቅድ ትውውቅ ማጠቃለያ መድረክ በደሴ ከተማ አካሂዷል።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቃልኪዳን ሽፈራው በመድረኩ ላይ እንደገለፁት፥ በክልሉ የተሻሻሉ አሰራሮችን በመጠቀም የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።
በዚህም በመኽር ወቅቱ ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታገጠም በማልማት 115 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም በምርት ወቅቱ አጠቃላይ 5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን ከ187 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ የተያዘውን ግብ ለማሳካት አጋዥ እንደሚሆን አስረድተዋል።
ከኩታ ገጠም አስተራረስ ባሻገር አሲዳማ መሬት በኖራ በማከም፣ግብዓት በማቅረብ፣መካናይዜሽንን በማስፋፋትና ሌሎችም ተግባራት በማከናወን የታቀደውን ምርት ለማግኘት ከወዲሁ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም በምግብ ራስን ለመቻል፣ለኢንዱስትሪ ጥሬ እቃና ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማምረት ግብርናው የሌሎች ኢኮኖሚ ዘርፎች መሰረት መሆኑን ለማረጋገጥ አላማ ያደረገ ነው ሲሉ አስታውቀዋል።
በመድረኩ የክልል፣የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራር አካላት፣ የግብርና ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026